43
ዜና ልማት ባንክ ZENA LEMAT BANK ሰኔ 2009 ዓ.ም ቁጥር 56 » የ82 ዓመቱ አዛውንት ባለሃብት (12) » Development Isuues (22) » 10 ስኬታማ ያልሆኑ መሪዎች ልማድ (26) » “የቤትህን አመል አዛው” ከማለት ባሻገር (35) Development Bank of Ethiopia Your Development Partner! www.dbe.com.et email: [email protected] Tel: +251 11551 1188/89 Fax: +251 11551 1606 Yosef Broz Tito Street P.O.Box: 1900 Addis Ababa, Ethiopia

ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

  • Upload
    others

  • View
    8

  • Download
    0

Embed Size (px)

Citation preview

Page 1: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክZ E N A L E M A T B A N K

ሰኔ 2009 ዓ.ም ቁጥር 56

» የ82 ዓመቱ አዛውንት ባለሃብት (12)

» Development Isuues (22)

» 10 ስኬታማ ያልሆኑ መሪዎች ልማድ (26)

» “የቤትህን አመል አዛው” ከማለት ባሻገር (35)

Development Bank of Ethiopia Your Development Partner!

www.dbe.com.etemail: [email protected]: +251 11551 1188/89Fax: +251 11551 1606Yosef Broz Tito StreetP.O.Box: 1900 Addis Ababa, Ethiopia

Page 2: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 10

የባንኩ ተልዕኮ፣ ራዕይና እሴቶች/ Mission, Vision and Values

ተልዕኮ/ Mission

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ልዩ የፋይናንስ ተቋም ሲሆን ተልዕኮውም የመንግስት የልማት አቅጣጫን መሠረት በማድረግ አዋጭ ለሆኑ የልማት ፕሮጀክቶች ከሀገር ውስጥና ከውጭ የብድር ገንዘብ በማሰባሰብ የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፍ መስጠት ነው፡፡ ይህንን ተልዕኮውንም ሲወጣ የባንኩን ህልውና በማረጋገጥ ጭምር ነው፡፡

ባንኩ ይህ ከፍተኛ ዋጋ ያለው ተልዕኮው እንዲሳካ ለቀጣይ አቅም ግንባታ ለደንበኛ ተኮር አገልግሎትና ለአካባቢ ጥበቃ ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣል፡፡

“The Development Bank of Ethiopia is a specialized financial institution established to promote the national development agenda through development finance and close technical support to viable projects from the priority areas of the government by mobilizing fund from domestic and foreign sources while ensuring its sustainability.

The Bank earnestly believes that these highly valued objectives can best be served through continuous capacity building, customer focus and concern to the wider environment”.

ራዕይ/ Vision

በባንኩ የፋይናንስ ድጋፍ የሚቋቋሙትን ፕሮጀክቶች በሙሉ እ.ኤ.አ. በ2ዐ2ዐ ላይ 1ዐዐ% ውጤታማ ማድረግ፡፡

“100% Success for All Financed Projects by 2020”

እሴቶች/ Values

ለተልዕኮአችን መሣካት ቁርጠኛ ነንለደንበኞቻችን ልዩ ትኩረት አለንሐቀኝነት ዋናው ሃብታችን ነውለቡድን ሥራ ትልቅ ቦታ እንሰጣለንሠራተኞች የባንኩ ተመን የሌላቸው ሀብት ናቸውሁሌም መማር የዕድገታችን መሠረት ነውለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት እንሰጣለን

Commitment to MissionCustomer focusIntegrityTeam workHigh value to employeesLearning organizationConcern to the environment

Development Bank of Ethiopia Your Development Partner!

Page 3: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ርዕሰ አንቀጽ

ዜና /መረጃ

ማስተዋወቂያ አምድ

ከደንበኞች ድምጽ » የ82 ዓመቱ አዛውንት ባለሃብት

» ሰማያታ እምነበረድ ፋብሪካ

ከሥራ ክፍሎቻችን

Development Issues

General Knowledge/ጠቅላላ እውቀት » 10 ስኬታማ ያልሆኑ መሪዎች ልማድ » የስራ ላይ ጫና ምንድነው? » Reviewing: the one minute manager » Time: the unnoticed resource » “የቤትህን አመል እዛው” ከማለት ባሻገር

ልዩ ልዩ » How to Be Happier in Your 20s » ግጥም

37

26

22

12

10

16

2

1

ማው

Page 4: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

የኤዲቶርያል ቦርድ አባላት ኃይሉ ምሥጋናው ሰብሳቢ አባቡ ካሳ አባል ጽጌ ገነት አባል አበባው ሲራጅ አባል አንተነህ መለሰ አባል ወርቁ ፈቃደ አባል ኃይሉ ታደሰ አባል ፍሬው መኳንንት ጸሐፊ

ዋና አዘጋጅ ፍሬው መኳንንት

አዘጋጅ መላኩ አላምረው

ፀሃፊ አለምጸሐይ ቀጸላ

ፎቶግራፈር ሀይሉ ታደሰ

ሌይዓውትና ዲዛይን ዳዊት ተስፋዬ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የልማት አጋርዎ !

Page 5: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

1ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ 107 ዓመት ዕድሜ ያለው አንጋፋ የፋይናንስ ተቋም ሲሆን የአጭር፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ ብድሮችን በመስጠት ይታወቃል። ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮም የመንግሥት የትኩረት አቅጣጫን በመከተል ለተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች የብድር አገልግሎት በመስጠትና የቴክኒክ ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛል።

የልማት ፕሮጀክቶችን የመደገፍ የዳበረ ልምዱን መሠረት በማድረግ በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን መንግሥት ለኢትዮጵያ ልማት ባንክ እ.ኤ.አ. ከጃንዋሪ 1 ቀን 2016 ጀምሮ ለሀገራችን አዲስ የሆነውን የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች እንዲሰጥ ከፍተኛ ኃላፊነትና ተልዕኮ ሰጥቶታል። ባንኩም የሀገሪቱን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ መሠረት በማድረግ የራሱን የአምሥት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ አዘጋጅቶ ወደ ሥራ ገብቷል። ዕቅዱን በመተግበር ውጤታማ መሆን ያስችለው ዘንድም የመዋቅርና የአደረጃጀት ለውጥ አድርጓል። ባንኩ ለግዙፍ ፕሮጀክቶች የሚሰጠውን ብድር የተሳለጠ ለማድረግ የባንኩ ካፒታል ከብር 3 ቢሊዮን ወደ ብር 7.5 ቢሊዮን እንዲያድግ ተደርጓል። ተደራሽነቱን ለማስፋትም አምሥት የነበሩትን ሪጅኖች ወደ 13 ዲስትሪክቶች እንዲሁም 32 የነበሩትን የባንኩ ቅርንጫፎች ወደ 110 አሳድጓል። የሰው ኃይሉን ለማጠናከር አዳዲስ ሠራተኞችን በመቅጠርና በማሰልጠን ብቁ ኃይል አሰማርቷል። አገልግሎቱን ለመስጠት የሚያስችሉ ቢሮዎችንና ፋሲሊቲዎችን በማሟላት ሥራ ላይ አውሏል።

ከዚህ በተጨማሪ በሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት ዙሪያ በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ዘዴዎችና የውይይት መድረኮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ። በአሁን ጊዜ በሚፈለገው ደረጃ ባይሆንም ደንበኞች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ጀምረዋል። ሆኖም በተያዘው በጀት ዓመትም ሆነ በቀሪዎቹ ሶስት የዕቅዱ ዓመታት ለዘርፉ የተነደፈው ስትራቴጂክ ዕቅድና የታሰበው ሰፊ የሥራ ውጥን ግቡን እንዲመታ ከባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅት በመፍጠር ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ተረባርቦ መሥራትን የሚጠይቅ ነው። በመሆኑም ባንኩ ይህን አገራዊ ተልዕኮ በግንባር ቀደምትነት በመምራትና በመተግበር ለዕቅዱ አፈጻጸም ቅድሚያ ተዋናይ መሆንና ለውጤት ማብቃት ይጠበቅበታል።

ባንኩ ከመንግሥት የተሰጠውን የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት ሥራን በአግባቡ እንዲወጣ ትኩረት

ሰጥቶ መሥራት ያስፈልጋል!

Page 6: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 2

The Development Bank of Ethiopia (DBE) and the Export - Import Bank of Korea (Eximbank) held Knowledge Sharing Program (KSP) here at the Head Office from May 30, 2017 to June 1, 2017.

Five high level expertise from Eximbank and 17 members of executives and middle level management members of the Bank were attended the meeting.

Objective of the meeting was establishing a knowledge-based development and economic cooperation between DBE and Korea’s Eximbank in strengthening capacity building, providing policy recommendations and organizing training programs.

During the meeting, DBE’s structure, the overall financing programs such as SME Lease Financing and Project Financing, technical operations, policies and procedures were introduced and presented by the Strategic Planning and Change Management Director of the Bank.

DBE, Eximbank Hold KSP

NEWS

Page 7: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 3

On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program (KSP), a knowledge-based development and economic cooperation program designed to share Korea’s development experience with partner countries such as Ethiopia. KSP offers comprehensive policy consultation tailored to the needs of partner countries encompassing in-depth analysis, policy recommendations and training opportunities, according to the presentation.

During the session, intensive discussions and question and answer program were conducted in relation to DBE’s role in the Ethiopian economic development, policies and strategies, SME financing, the overall

project work scope and schedule. Eventually, the two parties have signed Aide Memoire as an outline how to proceed in the future regarding the knowledge sharing program.

DBE has been providing credit services over the last ten decades in priority areas of the government such as commercial agriculture, agro processing industries, manufacturing industries and extractive and mining industries specifically export focused. While Eximbank has been providing comprehensive export loan and guarantee programs to support Korean enterprises’ including business overseas over the last four decades.

A senior Expert from Eximbank

Page 8: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et

ዜና / መረጃ

4

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የደንበኞች ምክክር መድረክ መጋቢት 02 ቀን 2009 ዓ.ም. በሒልተን አዲስ ሆቴል ተካሄደ።

የባንኩ ፕሬዝዳንት አቶ ጌታሁን ናና በመክፈቻ ንግግራቸው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የግሉን ዘርፍ በፋይናንስ የመደገፍ ኃላፊነት ተሰጥቶት የልማት ሥራዎችን ሲደግፍ መቆየቱንና አሁንም የድጋፍ ሥራውን የበለጠ አጠናክሮ መቀጠል እንዲችል ደንበኞች በፖሊሲና አሠራር ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን በመለየት አስተያየት እንዲሰጡበት መድረኩ መመቻቸቱን ገልጸዋል።

በመቀጠል ለውይይትና ምክክር የሚሆን መነሻ ጽሑፍ በስትራቴጂዊ ዕቅድና የለውጥ አመራር ዳይሬክቶሬት ቀርቧል። በዚህም የባንኩ ያለፉት ስድስት ዓመታት የሥራ አፈጻጸም፣ የባንኩ ፖሊሲዎችና አሠራሮች እንዲሁም ከዚህ ቀደም ከደንበኞች የቀረቡ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተዳሰዋል።

ባንኩ ባለፉት ስድስት ዓመታት ብር 50.6 ቢሊዮን አጽድቆ፣ ብር 32.3 ቢሊዮን ብር የለቀቀ ሲሆን ብር 21.45 ቢሊዮን ደግሞ መሰብሰቡ ተገልጿል።

ባንኩ የሀገር ውስጥ ባለሃብቶችን ለማበረታታት የብድር

ባንኩ ከደንበኞቹ ጋር ምክክር አደረገ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከፍተኛ እና መካከለኛ የሥራ አመራር አባላት ሚያዚያ 14 ቀን 2009 ዓ.ም. ለግማሽ ቀን የጥልቅ ተሃድሶ ውይይት አካሄዱ።

ውይይቱን የመሩት የባንኩ የቦርድ አመራር አባላት የሆኑት የተከበሩ አቶ ወንዱ ለገሠና የተከበሩ አቶ ስለሺ ለማ ናቸው።

አቶ ወንዱ በመክፈቻ ንግግራቸው ባንኩ በአገሪቱ ፈጣን ዕድገት እንዲመዘገብ በእርሻ፣ በኢንዱስትሪ እና በአገልግሎት ዘርፎች ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል፤ በመጫወትም ላይ ይገኛል፤ የዚህ ጥልቅ ተሃድሶ ውይይት ዓላማም የባንኩን ጠንካራና ደካማ ጎኖች በመለየት ጥንካሬውን የበለጠ ለማስቀጠልና ድክመቱን ደግሞ በማረም ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር ነው ብለዋል።

አቶ ስለሺ ለማ በበኩላቸው ጥልቅ ተሃድሶ በሀገር አቀፍ ደረጃ በስፋት በመካሄድ ላይ ይገኛል፤ ኪራይ ስብሳቢነትና ሙስና የበላይነትን ጨብጦ ሥርዓቱን እንዳያንገራግጨው ምንጮችን በማድረቅ ወደ ተሻለ ደረጃ መምጣት ያስፈልገዋል፤ የዛሬው ውይይትም የዚሁ አንድ አካል ነው በማለት ገልጸዋል።

በመቀጠል ለውይይቱ መነሻ የሚሆኑ ሁለት ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። በጽሑፎቹ ባንኩ ያለበት ሁኔታ እና በሥራ ሂደት ያጋጠሙ ችግሮች የተዳሰሱ ሲሆን የፖሊሲ፣ የመመሪያና የአሠራር ሂደቶችን ለማጥራት የተለያዩ እርምጃዎች መወሰዳቸውን፣ የእርሻ የብድር ፖሊሲ

ተከልሶ ወደ ሥራ መገባቱን፣ የመልካም አስተዳደርና የኪራይ ሰብሳቢነት ጉዳዮች፣ ባንኩን ወደፊት ለማራመድ ከከፍተኛውም ሆነ ከመካከለኛው የሥራ አመራር ብዙ እንደሚጠበቅ እና የመሳሰሉ ሃሳቦች ቀርበዋል።

በማስከተል ሰብሳቢዎቹ መድረኩን ለውይይት፣ ጥያቄና አስተያየት ክፍት አድርገዋል። ከቤቱ ከተነሱ ሀሳቦች መካከል ውይይቱ በዚህ መልክ መካሄዱ ጥሩ እንደሆነ፣ በባንኩ በርካታ በጎ ሥራዎች ከዚህ ቀደም መሠራታቸውንና አሁንም በመሠራት ላይ እንደሚገኙ መገለጽ እንደሚኖርበት፣ ከባለድርሻ አካላትና ደንበኞች የሚመጡ ግፊቶች ባንኩን አጣብቂኝ ውስጥ እንደሚከቱት፣ አሰራራችንን በጥራት እያካሄድን መሆን አለመሆኑን በሚገባ መፈተሽ እንደሚያስፈልግና ለዚህም በስትራቴጂ የተደገፈ መፍትሔ እንደሚያሻ እንዲሁም ሌሎች ጠቃሚ ሀሳቦች ተሰንዝረዋል።

በመጨረሻም ሰብሳቢዎቹ አብዛኛዎቹ ከቤቱ የተነሱት ሀሳቦች የጋራ ግንዛቤ የተወሰደባቸው መሆናቸውንና ይህም የበታች ሠራተኛው ድረስ መዝለቅ እንደሚኖርበት፣ ለመለወጥ በመጀመሪያ ራስን መመልከት እንደሚያስፈልግ፣ ለችግሮች መነሻ የሚሆኑ ጉዳዮችን መለየት መፍትሔ ለመስጠት ትልቅ አቅም እንደሚሆን ለዚህም የአመለካከት ለውጥ እንደሚያስፈልግ፣ ተሃድሶ ማለት የአንድ ቀን ሥራ ሳይሆን ሂደት መሆኑን አብራርተው ውይይቱን ቋጭተዋል።

ባንኩ የጥልቅ ተሃድሶ ውይይት አካሄደ

Page 9: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 5

ፖሊሲውን 25፡75 ማድረጉ፣ የዓይነት መዋጮ ግምት ውስጥ ማስገባቱና የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች መስጠት መጀመሩ ትልቅ እመርታ መሆኑ በጽሑፉ ተመላክቷል። በተጨማሪም አጠቃላይ የባንኩ የብድር መስተንግዶ አሠራር፣ የአጭር ጊዜ ብድር መቋረጥ፣ የLC ሂደት ፈጣን አለመሆን፣ የዲስትሪክቶች የብድር ጣሪያ አነስተኛ መሆን፣ የእርሻ ብድር መቆም የመሳሰሉት ከዚህ ቀደም በደንበኞች ተነስተው የነበሩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ሲሆኑ አሁን ግን ምላሽ ያገኙ መሆናቸውንና በአንዳንዶቹም ላይ ለውጥ ለማምጣት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ተብራርቷል።

ከቀረበው የመወያያ ጽሑፍ በኋላ የባንኩ ፕሬዝዳንት መድረኩን ለውይይትና ምክክር ክፍት አድርገዋል።

በዚህም ከደንበኞች የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶን ተነስተዋል። ከእነዚህም መካከል ባንኩ ከመሬት አስተዳደር፣ ከመድን ዋስትናና ከጸጥታ አካላት የመሳሰሉ ባለድርሻዎች ጋር በቅንጅት ቢሠራ፣ የማስፋፊያ ብድር መዋጮ ስሌት ቢስተካከል፣ የጥናት ግምገማ ወቅታዊ ዋጋዎችን መሠረት ያላደረገ መሆኑ፣ የለማ መሬት የመዋጮ ግምት ውስጥ አለመግባት፣ በቋሚ ተክሎችና በአንዳንድ መስኮች የባለሙያ ችግር ያለበት መሆኑ፣ የፖሊሲና አሠራር ችግሮች ስለመኖራቸው፣ የእፎይታ ጊዜ ብድር ቢራዘም፣ ሴት አልሚዎችን ለማበረታታት ጥረት አለመኖሩ፣ የወለድ

ምጣኔ በድንገት መጨመርና፣ የብድር አለቃቀቅ ቅደም ተከል ላይ ስላሉ ችግሮች ተነስተዋል።

በመጨረሻም የባንኩ ፕሬዝዳንት የተሰጡ አስተያየቶች ገንቢ መሆናቸውንና በሶስት ጉዳዮች ማለትም በፖሊሲ፣ በአሠራርና በቅንጅት ዙሪያ ያጠነጠኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም የፕሪሽመንትና ምርቶቻቸውን ወደ ውጭ የሚልኩ ባለሀብቶችን ለማበረታታት የተቀመጠው የወለድ ምጣኔ አነስተኛና ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ተመሳሳይ እንደሆነ፣ የእፎይታና የብድር ክፍያ ጊዜ እንዲሁም ተያያዥ ጉዳዮች የሚመሠረቱት በቀረበው ጥናት ላይ እንደሆነ፣ የሥራ ማስኬጃ ብድርን በሚመለከት ለመንግስት መቅረቡን፣ የለማ መሬትና አጠቃላይ የጋምቤላን ጉዳይ በሚመለከት በሌላ መድረክ በድጋሚ እንደሚታይ ተናግረዋል።

አቶ ጌታሁን አጠቃላይ የባንኩን አሠራር በሚመለከት ወደ ውስጥ መፈተሸ እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መሥራት እንደሚያስፈልግ እንዲሁም በመድረኩ የተነሱ ጠቃሚ ሀሳቦች እንዳለ መወሰዳቸውን ገልጸው ስብሰባውን ደምድመዋል።

በዚህ የውይይት መድረክ ላይ ከ200 በላይ ደንበኞች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት እና የባንኩ ደንበኞች በውይይት ላይ

Page 10: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et

ዜና / መረጃ

6

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ጌታሁን ናና ባንኩ እያስመዘገበ ካለው ዝቅተኛ አፈፃፀም ተመልሶ ከፍ ወዳለ ደረጃ እንዲሸጋገር መላው ሠራተኛ ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት እንዳለበት ማሳሰቢያ ሰጡ፡፡

ፕሬዝዳንቱ ይህንን ማሳሰቢያ የሰጡት ጥር 29 ቀን 2009 ዓ.ም በካፒታል ሆቴል በተካሄደው የባንኩ የ2009 በጀት ዓመት 2ኛው ሩብ ዓመት የማኔጅመንት አባላት ስብሰባ ላይ ነው፡፡

በዚህ የማኔጅመንት ስብሰባ ላይ የባንኩ የ2ኛው ሩብ ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት በስትራቴጂክ ፕላኒንግ እና ለውጥ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን አፈጻጸሙም ዝቅተኛ መሆኑ ተገምግሟል፡፡ በሪፖርቱ መሠረት ባንኩ በሩብ ዓመቱ ብር 5.3 ቢሊዮን ለመፍቀድ አቅዶ ብር 3.7 ቢሊዮን (71%) ፈቅዷል፡፡ ለመልቀቅ ካቀደው ብር 3.9 ቢሊዮን ውስጥም ብር 1.6 ቢሊዮን (የዕቅዱን 41%) ለፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ ወጪ አድርጎ ሰጥቷል፡፡ ከተበዳሪዎች ለመሰብሰብ ካቀደው ብር 1.3 ቢሊዮን ውስጥም ብር 0.88 ቢሊዮን (የእቅዱን 68%) ነው ለማሳካት የቻለው፡፡ በዚህ መሠረት ባንኩ በበጀት ዓመቱ የ2ኛው ሩብ ዓመት ያስመዘገበው አፈጻጸም ከዕቅዱ እንዲሁም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ጋር ሲነፃፀር ዝቅተኛ መሆኑ ተገምግሟል፡፡

በዕለቱ የባንኩ ፕሬዝዳንት አቶ ጌታሁን ናና በአጽንዖት እንደገለጹት አንጋፋው የሀገር ልማት አጋር የአትዮጵያ ልማት ባንክ በአሁኑ ሰዓት በሁለንተናዊ አፈጻጸሙ እየተዳከመና ከነበረበት ዝናው እየወረደ ከትርፋማነት ይልቅ ወደ ኪሳራ እያመራ ስለሆነ ከዚህም በላይ ወደ ባሰ ውድቀት ከመሄዱ በፊት ሁላችንም የተጣለብንን ሕዝባዊና

ሀገራዊ ኃላፊነት በአግባቡ ልንወጣ ይገባል ብለዋል፡፡ ባንኩ በዋናነት የፖሊሲ፣ የመመሪያ፣ ፕሮሲጀርና የጋይድላይን ችግር እንደሌለበትና ችግሩ የመነጨው ይህንን ተከትሎ በአግባቡ ካለመስራት እንደሆነ የገለጹት ፕሬዝዳንቱ ሁሉም ሠራተኛ በየደረጃው ራሱን ከግላዊ ጥቅም ፈላጊነት ነጻ በማድረግና በባለቤትነት ስሜት ሕጋዊ አሠራሮችን ብቻ ተከትሎ በመሥራት ባንኩን ከተጋረጠበት ችግር ለማዳንና ለውጥ ለማምጣት መነሳሳት እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡

አቶ ጌታሁን አያይዘውም በአሁኑ ሰዓት በፕሬዝዳንት ጽ/ቤት አንድ ልዕለ ደረጃ (High Level) ኮሚቴ እንደተዋቀረና ኮሚቴውም አጠቃላይ የባንኩን የፖሊሲ፣ ደንብና መመሪያ ጥሰት ፈትሾና ለይቶ እንደሚያቀርብ፣ በግኝቱ መሠረትም በየደረጃው ተገቢው የእርምት እርምጃ እንደሚወሰድ አስገንዘበዋል፡፡

ይህንን ዝቅተኛ የአፈጻጸም ሪፖርት ያዳመጡት የማኔጅመንት አባላት በውይይት ወቅት በሰጡት አስተያየት ባንኩን ከውድቀት ለመታደግና ወደ ተሻለ የከፍታ ደረጃ ለመመለስ በሚያስችሉ የመፍትሔ እርምጃዎች ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን የብድር ክትትል ውጤታማነት፣ የተበላሹ ብድሮችን መቀነስ፣ የእርሻ ብድር መጀመር፣ የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎትና የመልካም አስተዳደር በትኩረት ከተዳሰሱ ጉዳዮች ዋና ዋናዎቹ ነበሩ፡፡

በመጨረሻም አባላቱ “የለውጥ ጊዜው አሁን ነው! ለባንኩ ውድቀትም ሆነ ትንሣኤ ኃላፊነቱ የእኛው ነው! ለሚፈጠሩ ችግሮች ሁሉ ወደ ውጭ ከመጠቆም ይልቅ ወደ ራሳችን እንመልከት!” ያሉ ሲሆን በተነበበው የአቋም መግለጫም በአንድ ድምጽ “ለውጥ ከራስ ይጀምራል!” በማለት ጉባኤው ተጠናቋል፡፡

ባንኩን አሁን ካለበት ወደተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር ጠንክሮ መሥራት ያስፈልጋል - ፕሬዝዳንት

Page 11: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 7

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የመሠረት ድንጋይ የተጣለበትን ስድስተኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ የታላቁ ሕዳሴ ቦንድ ሽያጭ ሣምንት የካቲት 20 ቀን 2009 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተካሄደ።

ሥነ ሥርዓቱን በይፋ የከፈቱት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ድሪባ ኩማ ሲሆኑ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የመንግስት ባለሥልጣናትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በቦታው ተገኝተዋል።

የዕለቱ የክብር እንግዳ አቶ ድሪባ ኩማ በመክፈቻ ንግግራቸው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የመሠረት ድንጋይ ከተጣለበት ዕለት አንስቶ እስካሁን ድረስ የፋይናንስ፣ የቴክኒክና የሀሳብ ድጋፍ ላደረጉ ተቋማትና የሕብረተሰብ ክፍሎች ምስጋናቸውን አቅርበው ይህ የቦንድ ሽያጭ ሣምንት ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን /ማርች 8 በሚከበርበት ጊዜ መካሄዱም ልዩ እንደሚያደርገው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክም የቦንድ ሽያጭ ሣምንቱ የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት በተሳካ ሁኔታ እንዲካሄድ ሙሉ በሙሉ ወጪውን የሸፈነ ሲሆን ባንኩም ለዚሁ ዓላማ ተብለው በተተከሉ ድንኳኖች በመገኘት የቦንድ ሽያጭ ማከናወን ጀምሯል።

የዕለቱ የክብር እንግዳ ከንቲባ ድሪባ ኩማም የጥብጣብ ቆረጣ ሥነ ሥርዓቱን አከናውነው ቦንድ በመግዛት አርዓነታቸውን አሳይተዋል።

በተጨማሪም ባንኩ የህብረተሰቡን ግንዛቤ ይበልጥ ለማሳደግ

እንዲሁም የሚሰጠውን አገልግሎን ለማስተዋወቅ ያስችለው ዘንድ ስለ ቦንድ ምንነት እና ጠቃሚነት የሚያስተዋውቁ ልዩ ልዩ የህትመት ውጤቶችን ማለትም የቦንድ ብሮሸሮችን፣ በራሪ ወረቀቶችን፣ ፖስተሮችንና ባነሮችን በማሰራጨት ላይ ይገኛል።

የቦንድ ሽያጭ ሣምንቱ ከየካቲት 20 - 29 ቀን 2009 ዓ.ም. ድረስ በመላ አገሪቱ በተተከሉ የመሸጫ ጣቢያ ድንኳኖች በመከናወን ላይ ይገኛል።

የቦንድ ሽያጭ ሣምንት ተካሄደ

በመንግሥት ፋይናንስ ድርጅቶች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ስንታየሁ ወልደ ሚካኤል ፊርማ ታኅሣሥ 10 ቀን 2009 ዓ.ም. ለኢትዮጵያ ልማት ባንክ በተላከ ደብዳቤ ከዚህ ቀደም የባንኩ የቦርድ አመራር ሰብሳቢ የነበሩት ክቡር አቶ አህመድ አብተው በነበራቸው የኃላፊነት ዘመን ላበረከቱት አስተዋጽኦ ተመስግነው ተሰናብተዋል፡፡ በምትኩም ክቡር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ቀጣዩ የባንኩ የቦርድ አመራር ሰብሳቢ ሆነው ተመድበዋል፡፡

በተያያዘም ከዚህ ቀደም የቦርድ አመራር አባላት የነበሩት አቶ አያና ዘውዴ፣ አቶ ሬድዋን ሁሴን፣ አቶ ያዕቆብ ያላ እና አቶ ቶሎሳ ሻጊ ከምስጋና ጋር የተሰናብቱ ሲሆን በምትካቸውም አቶ ቴዎድሮስ ገ/እግዚአብሔር፣ አቶ ወንዱ ለገሠ እና አቶ ደሳለኝ አምባው አዲስ የቦርድ አመራር አባላት ሆነው ተመድበዋል፡፡

ለባንኩ አዲስ የቦርድ አመራር አባላት ተመደቡ

አቶ ሽፈራው ሽጉጤ የባንኩ ቦርድ ሰብሳቢ

Page 12: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et

ዜና / መረጃ

8

ብርሃን ኢንሹራንስ አ.ማ. ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ጥቅምት 30 ቀን 2009 ዓ.ም. የሰባት ሚሊዮን ብር ቦንድ ገዛ።

የብርሃን ኢንሹራንስ አ.ማ. ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ተፈራ በሥነ ሥርዓቱ ላይ እንደተናገሩት ድርጅታችን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሕልውና አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ለሚታመነው ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከዚህ ቀደም ገዝቶት ከነበረው በተጨማሪ በዛሬው ዕለት የሰባት ሚሊዮን ብር ቦንድ ገዝቷል።

ማኔጂንግ ዳይሬክተሩ ይህም በመላው ሕዝብ ተስፋ የተጣለበት ግድብ ፍጻሜ ሲያገኝ አገሪቱን በልማት ጎዳና አንድ እርምጃ ወደፊት ያራምዳታል የሚል እምነት አለን ብለዋል።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የፋይናንስና ባንኪንግ ምክትል ፕሬዝዳንት ወ/ሮ አልማዝ ጥላሁን በበኩላቸው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ቀጣይነቱ ተጠብቆ እስከፍጻሜው እንዲደርስ ተነሳሽነት ይፈልጋል፤ በዚሁ መሠረት የብርሃን ኢንሹራንስ አ.ማ. በራሱ ተነሳሽነት ይህን ቦንድ በመግዛቱ ሊመሰገን ይገባዋል በማለት ተናግረዋል።

ምክትል ፕሬዝዳንቷ የኢትዮጵያ ልማት ባንክም ግድቡ ከፍጻሜ እንዲደርስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ

እንደሚገኝና ጅምር ሥራውም ፍሬ አፍርቶ እድንናይ ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል የበኩሉን አስተዋጽኦ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪዬን አቀርባለሁ ብለዋል።

በቦንድ ሽያጩ ርክክብ ሥነ ሥርዓት ላይ የኮርፖሬት ማስተዋወቅና ግንኙነት ዳይሬክቶሬት እንዲሁም የኮርፖሬት ቦንድ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በዓለም አቀፍ ከታወቁ አምስት ተወዳዳሪዎች መካከል በጨረታ አሸናፊ ከሆነው የጃፓኑ የግል ኩባንያ Juki Singapore PTE LTD ጋር ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች አቅርቦት የሚውል የልብስ ስፌት ማሽን በ1.5 ሚሊዮን ዶላር የጥቅል ግዥ ኮንትራት ስምምነት ታህሳስ 20 ቀን 2009 ዓ.ም. ተፈራረመ።

የጥቅል ግዥ ኮንትራት ስምምነቱን የፈረሙት

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሊዝ ፋይናንሲንግ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ተሾመ አለማየሁ እና የጃፓኑ Juki Singapore PTE LTD ዳይሬክተር Mr. Noriak Sai-to ናቸው።

አቶ ተሾመ የኮንትራት ስምምነት የተካሄደባቸው ማሽነሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለተለዩ ክላስተሮች የተዘጋጁ መሆናቸውንና የደንበኞች ምልመላም እየተካሄደ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ከጥቅል ግዥ ጠቀሜታዎች ውስጥ የዓለም አቀፍ ጨረታ ግዥ ሥርዓት ረጅም ጊዜ የሚወስድ በመሆኑ የደንበኞችን ፍላጎት መሠረት በማድረግ አስቀድሞ ቢከናወን በቶሎ ወደ ሥራ ለመግባት ማስቻሉ፣ የግዥ ሥርዓት ብዙ የሎጀስቲክስ ጉዳዮች ስላሉት ግዥው በጥቅል ሲፈጸም ከዋጋም ሆነ ከጊዜ አኳያ አዋጭ መሆኑ፣ ከተናጠል ይልቅ በብዛት ለሚታዘዙ ማሽኖች የሚሰጥ ዋጋ ቅናሽ ያለው መሆኑና ተወዳዳሪዎችም ጨረታውን ለማሸነፍ ውድድር ውስጥ ስለሚገቡና ለማሸነፍም ዝቅተኛ ዋጋ ማቅረባቸው ዋና ዋናዎቹ ናቸው።

ባንኩ የ1.5 ሚሊዮን ዶላር ጥቅል ግዥ ኮንትራት ተፈራረመ

ብርሃን ኢንሹራንስ አ.ማ. የ7 ሚሊዮን ብር ቦንድ ገዛ

Page 13: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 9

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ተሳታፊ የሆነበት ሁለተኛው ዙር አገር አቀፍ የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ኢግዚቢሽን እና ባዛር ከግንቦት 24-30/2009 ዓ.ም. ሜክሲኮ በሚገኘው የፌዴራል አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች ልማት ኤጀንሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ተካሄደ።

ግንቦት 24 ቀን 2009 ዓ.ም. በተካሄደው የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሊዝ ፋይናንሲንግ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ተሾመ አለማየሁን ጨምሮ የፌዴራል አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች ልማት ኤጀንሲ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የኤግዚቢሽኑ ተሳታፊዎችና የሚዲያ አካላት ተገኝተዋል።

ሥነ ሥርዓቱን በንግግር መርቀው የከፈቱት የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ አስፋው አበበ ሲሆኑ የኤግዚቢሽንና ባዛሩ ዓላማ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን የሚደግፉ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የሚሰጡትን አገልግሎት ለተሳታፊዎች ማስተዋወቅና የልምድ ልውውጥ እንዲያደርጉም ምቹ ሁኔታን መፍጠር ነው ብለዋል።

ኤግዚቢሽንና ባዛሩ “የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ለዘላቂ ልማት!” በሚል መሪ ቃል በመካሄድ ላይ ሲሆን ከዘጠኙ ክልሎችና ከሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች

የተውጣጡ ከ100 በላይ የአነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ተሳትፈዋል።

ባንኩም ይህን ዕድል በመጠቀም የተለያዩ የህትመትና የፕሮሞሽናል ቁሳቁሶችን በማሰራጨት ጭምር ባንኩ የሚሰጣቸው አገልግሎቶች በተለይም የሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎትን በስፋት አስተዋውቋል።

ባንኩ ተሳታፊ የሆነበት 2ኛው ዙር ኢግዚቢሽንና ባዛር ተካሄደ

በኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት መሠረት የሰባት ሚሊዮን ብር የማሽነሪ ግዥ ከቻይና ሀገር የተፈጸመለት ቅባት ማምረቻ ኢንተርፕራይዝ ሥራ ጀመረ።

ፋብሪካው በኦሮሚያ ክልል ሱሉልታ ከተማ ማርታና አብነት የውበት ቅባት ኢንተርፕራይዝ በሚል ሥም የተቋቋመ ሲሆን ሥራ መጀመሩን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ የሚዲያ አካላት ታህሳስ 21 ቀን 2009 ዓ.ም. ፋብሪካውን ጎብኝተው ዘገባውን ለኅብረተሰቡ እንዲያደርሱ ተደርጓል፡፡

የኢንተርፕራይዙ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ አብነት ቱሉ ድርጅቱ በ2004 ዓ.ም. ከብድርና ቁጠባ ተቋማት ባገኘው የብር 5‚000 ብድር የተለያዩ የመዋብያ ቅባቶች ማምረት መጀመሩን እና ከጥቃቅንና አነስተኛ ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ በማደግ ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ድጋፍ ማግኘታቸውን ገልጸዋል፡፡

ፋብሪካው የተለያዩ መጠን ያላቸውን ምርቶች፣

የመዋብያ ቅባቶችና ማሸግያ ፕላስቲኮችን በማምረት ከውጭ ሀገር ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ ተመሳሳይ ምርቶችን በመተካት የውጪ ምንዛሪ በማዳን ላይ እንደሚገኝም ሥራ አሥኪያጁ ተናግረዋል፡፡

ፋብሪካው ሥራ ሲጀምር በቀን 1‚000 ያመርት እንደነበረና በአሁኑ ጊዜ አቅሙን በማሳደግ ከ40‚000 በላይ ፍሬዎችና ሌሎች ቅባቶችን በማምረት ከፍተኛ ገቢ እያገኘ መሆኑንና ከ50 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩንም አብራርተዋል፡፡

እንደ አቶ አብነት ገለጻ ፋብሪካው 1550 ካ.ሜ ቦታ ላይ ያረፈ ሲሆን ወደፊትም አሁን በተፈጠረው ጥሩ የገበያ ትስስር በመጠቀም በተሻለ ጥራትና ብዛት ምርቶቹን ገበያ ላይ ለማቅረብ ፋብሪካው ለኢትዮጵያ ልማት ባንክ የ23 ሚሊዮን ብር ፕሮፓዛል አቅርበው በመጠባበቅ ላይ እንደሆኑ ገልፀዋል፡፡ አጠቃላይ የኢንተርፕራይዙ ካፒታልም 20 ሚሊዮን ብር መድረሱን አቶ አብነት አክለው ገልጸዋል፡፡

የሰሜን አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ መኮንን ጃለታ በበኩላቸው ማርታና አብነት የውበት ቅባት ኢንተርፕራይዝ በኢትዮጵያ ልማት ባንክ የቀረበውን የዱቤ ግዥ ኪራይ አገልግሎት ተጠቃሚ በመሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለውጤት እንደበቃና ለሌሎች ዜጎችም የሥራ ዕድል በመፍጠር አርአያ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም ሥራ አስኪያጁ ባንኩ 17 ለሚሆኑ ባለሀብቶች በ191 ሚሊዮን ብር የማሽነሪ ግዥ ፈቅዶ በሂደት ላይ እንደሚገኝና ስለ አገልግሎቱ በስፋት የማስተዋወቅ ሥራም በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

በባንኩ የማሽነሪ ግዥ የተፈጸመለት መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ሥራ ጀመረ

Page 14: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 10

የሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ (2008-2012) በመሠረቱ የመጀመሪያውን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ መነሻዎች፣ ዓላማዎችና የትኩረት አቅጣጫዎች የሚያስቀጥል ሆኖ በመጀመሪያው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ አፈፃፀም ሒደት የተመዘገቡ ውጤቶች፣ በአፈፃፀም ሒደት ያጋጠሙ ፈታኝ ሁኔታዎችና መልካም ተሞክሮዎች እንደ መነሻ ተወስደዋል፡፡ ይህም ሆኖ ሁለተኛውን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ልዩ ትኩረት የሚደረግባቸው ጉዳዮች አሉ፡፡ እነዚህም እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡

ሀ) ግብርና በዚህ ዕቅድ ዘመንም ለልማታችንና ፈጣን ዕድገታችን የማይተካ አስተዋፅኦ የሚያደርግና የዘመናዊ አምራች ዘርፍ ዕድገት ዋና ምንጭ ሆኖ ይቀጥላል፡፡ ከዚህ አኳያ ለውጥ ማምጣት የጀመሩትን የስትራቴጂክ የምግብ ሰብሎች ምርታማነትና ጥራት የበለጠ ከማሳደግ በሻገር የላቀ ዋጋ የሚያወጡ የኢንዱስትሪ ግብዓቶችና የወጪ ንግድ ምርቶች ላይ የልማት ቀጠናን ማዕከል ያደረገ ርብርብ በማድረግ ልዩ ትኩረት ይሰጣል፡፡ በዚህም መሠረት የመስኖ ግብርና፣ የአበባ፣ የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ሥራን በከፍተኛ ደረጃ ማስፋፋት ላይ ልዩ ትኩረት ይሰጣል፡፡ በምርት ሂደት ውስጥ ተዋናይ የሆኑ የአርሶ-አደሩና የአርብቶ-አደሩ የቤተሰብ ግብርና ተጠናክሮ የሚቀጥል ሆኖ ለአርሶ-አደሩ የተማሩ ወጣቶችና የግል ባለሀብቱ ቅንጅት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ይሠራል፡፡ ይህንን ለማድረግም በግብርና ልማትና ግብይት ውስጥ ያሉ የሥርዓት ማነቆዎችን በአስተማማኝ ደረጃ መፍታት ልዩ ትኩረት የሚሰጠው ይሆናል፡፡

ለ) ራሱን የቻለ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት ራእይ መቀመጡና ላለፉት 1ዐ ዓመታት በተከታታይ የተመዘገበውን ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ለማስቀጠልና የመካከለኛ ገቢ ራዕዩን ለማሣካት በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሚመዘገበው እመርታና ከዚሁ ጋር በኢኮኖሚው አወቃቀር ላይ የሚጠበቀው ለውጥ በቀጣዩ አምስት ዓመት የልማት ዕቅድ ዘመን ልዩ ትኩረት የተሰጠው መሆኑ፣

ሐ) የኢኮኖሚው የማምረት አቅም ላይ ለመድረስ ቅልጥፍና መጨመርና የአምራች ዘርፎች /ማኑፋክቸሪንግ እና ግብርና/ በሚመረቱ ምርቶች ለጥራት፣ ለምርታማነት እና ተወዳዳሪነት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራና ይህንንም ለማስፈፀም ቀደም ብሎ በመጀመሪያው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ዘመን የተጀመረው ካይዘን በስፋትና በጥልቀት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል፣ የቤንች ማርኪንግ እንቅስቃሴም እንደሚስፋፋ ግልፅ ግቦች መቀመጣቸው፣

መ) በጠቅላላ ፍላጎትና አቅርቦት መካከል ለሚታየው መዛባት ልዩ ትኩረት መሰጠቱና ፈጣን እድገት የማስመዝገብ ግብም ይህን የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት ከማስተካከል አኳያ እንዲቃኝ ለማድረግ ልዩ ትኩረት

መሰጠቱ ነው፡፡ በዚህ ረገድ ይህ መዛባት ሁሉት መልክ አለው፡፡ በቁጠባና በኢንቨስትመንት መካከል ያለው ክፍተት በየጊዜው እየሰፋ መሄዱና በሌላ መልኩ ደግሞ በወጪና በገቢ ንግድ መካከል ያለው ክፍተት እየሰፋ መሄዱ ናቸው፡፡ እነዚህ ደግሞ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸው፡፡ በመሆኑም ይህን መዛባት ለማስተካከል የግልና የመንግስት ቁጠባን የማስፋፋትና የወጪ ንግድ ምርቶችን ምርታማነት ጥራትና ተወዳዳሪነት የማሣደግ እንቅስቃሴ ከመቸውም ጊዜ የላቀ ጥረት እንደሚጠይቅና ይህንንም ለማሳካት ግልፅ ግቦች መቀመጣቸው፣

ሠ) የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ልማትና ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት አቅምን የማጎልበት ስራ በአግባቡ ለመምራት የሚያስችል የፖሊሲና ስትራቴጂ ማዕቀፍ መዘጋጀቱና ይህም በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው በተለይ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን /የግድቦች ግንባታ፣ የመንገድ ግንባታ፣ የመስኖ ግንባታ… ወዘተ/ የማስተዳደርና የመምራት እንዲሁም በተያዘላቸው ወጪ እና ጊዜ የመፈፀም አቅም እስካሁን በተገኘው ተሞክሮም በተሻለ ደረጃ ላይ እንዲደርስ ግብ መጣሉ፣

ረ) የከተማነት መስፋፋት ፈጣን እድገትና መዋቅራዊ ለውጥ አስተዋፅኦ የጎላ እንዲሆን ለማስቻል እና ከሚጠበቀው ፈጣን ኢንዱስትራላይዜሽን እንቅስቃሴ ጋር ለማጣጣም ለከተማ አስተዳደርና አመራር ልዩ ትኩረት መሰጠቱ፣

ሰ) ለሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች ትራንስፎርሜሽን ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል፡፡ ይህም በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ በተለይም ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ምርቶችን በማምረት ላይ ለሚገኙት ተቋማዊ፣ ሪጉላቶሪና የፋይናንስ ድጋፍ በመስጠት አቅማቸውን በማሳደግ (ምርታማነት፣ ጥራትና ተወዳዳሪነት) እና በአገልግሎት ዘርፍ የተሰማሩትን ደግሞ ልዩ ልዩ ማበረታቻዎችን በመስጠት ወደ አምራች ዘርፉ (ማኑፋክቸሪንግ) እንዲገቡ በማድረግ የሚገለፅ ነው፡፡ በተጨማሪም በአነስተኛና ጥቃቅን ደረጃ የሚገኙትን ኢንተርፕራዞች ወደ መካከለኛ እና ከፍተኛ ማኑፋክቸሪንግ የማሸጋገርና በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩትን ደግሞ በተደራቢ ለራሳቸቸው የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን በማምረት የገቢ ምርትን በመተካት ላይ እንዲያተኩሩ አስፈላጊውን ድጋፍ በመስጠት ይገለፃል፡፡ የሀገር ውስጥ ባለሀብቱን እንዳመችነቱ ከውጭ ባለሀብቱ ጋር በማቀናጀት የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማፋጠን ይገለፃል፡፡

ሸ) የተጀመረውን ፈጣን ዕድገት ለማስቀጠል የሰው ኃብት ልማቱን በቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ እንዲደገፍ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል፡፡ በዚህ ረገድ ዋናው ጉዳይ የትምህርትና ጤና አገልግሎትን ተደራሽነት እና ጥራት በማረጋገጥ የሥራ ኃይሉን የተማረና ጤናማ ከማድረግ በተጨማሪ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እንዲጠቀም በማስቻል ጥራቱን በማሳደግ ዕውቀት ያለውና ተወዳዳሪ የሥራ ኃይል

የሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ልዩ የትኩረት መስኮች

ማስተዋወቂያ አምድ

(2008-2012)

Page 15: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 11

በመፍጠር ለሚጠበቀው ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ቁልፍ ሚና እንዲጫወት ማስቻል ነው፡፡ በመሆኑም ከሀገሪቱ የዕድገት ፍላጎት ጋር የተጣጣመ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማፋጠን ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ይሠራል፡፡

ቀ) ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ይሠራል፡፡ በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማት ስትራቴጂን በማዘጋጀትና በመተግበር ግንባር ቀደም ናት፡፡ ከዚህ አንፃር የአካባቢ ሙቀት ሳቢ ጋዞችን ልቀት በመቀነስ አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባት የእንስሳትና የሰብል ምርታማትን በማሳደግ የአርሶ/አርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ፣ የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ ደንን መጠበቅና ማልማት፣ ከታዳሽ ኃይል ምንጭ የኤሌክትሪክ ኃይል በሰፊው ማመንጨትና ዘመናዊና ኃይል ቆጣቢ ቴክኖሎጂዎችን በትራንስፖርት፣ በኢንዱስትሪና በህንፃ ኮንስትራክሽን ዘርፎች በመጠቀም ረገድ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ ይሠራል፡፡

በ) ከላይ የተዘረዘሩ ሥራዎችን ስንሠራ የፖለቲካ ኢኮኖሚው ኪራይ ሰብሳቢነት የበላይነት ከያዘበት ወደ ልማታዊ ፖለቲካል ኢኮኖሚ የበላይነት ወደያዘበት ትራንስፎርሜሽን እንዲለወጥ ማድረግ የሞት ሽረት ሥራ የሆነበት የዕቅድ ዘመን ነው፡፡ ከዚህ አኳያ በአንድ በኩል ልማታዊነትን የሚያጐለብቱ ድጋፎችን በጥራት በማቅረብ በሌላ በኩል የኪራይ ሰብሳቢነት ዋነኛ ምንጭ ሆነው የተለዩትን ጉዳዮች በልዩ ትኩረት በማድረቅ ኪራይ ሰብሳቢነት፣ ሙስናና ብልሹ አሠራሮችን በቁጥጥር ሥር በማዋል ልማታዊነት የበለጠ እንዲጐመራና የበላይነት እንዲይዝ የሚደረግ ይሆናል፡፡ ይህ እንዲሆንም ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ይሠራል፡፡ ህዝባችን የሥራው ባለቤት ሆኖ እንዲሠማራ ይደረጋል፡፡

ከዚህ በላይ የተመለከቱት የሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የትኩረት መስኮች ከዚህ በታች ቀጥሎ በቀረቡት የዕቅዱ ዓላማዎች፣ መሠረታዊ አቅጣጫዎች እና በቀጣይም በማክሮ-ኢኮኖሚና በዘርፉ ዕቅዶች ቀርበዋል፡፡

የዕቅዱ ዓላማዎች

የሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዓላማዎች እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር በ2017 ሀገራችንን ዝቅተኛ መካከለኛ ገቢ (Lower Middle Income) ካላቸው ሀገሮች ተርታ ለማሰለፍ የተቀመጠውን ሀገራዊ ራዕይ ለማሳካት የተጀመረውን ፈጣን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽንና ሕዳሴ ጉዞ በላቀ ደረጃ ለመፈፀም የሚያስችሉ ይሆናሉ፡፡ በዚህም መሠረት ዕቅዱ የሚከተሉት ዋና ዋና ዓላማዎች አሉት፡፡

ሀ) የተረጋጋ ማክሮ-ኢኮኖሚ በመከተል በኢኮኖሚው መታየት የጀመሩትን የሚዛን ክፍተቶች በማስተካከል ኢኮኖሚውን በአማካይ በ11 በመቶ ማሳደግና ለሀገሪቱ ራዕይ መሳካት አስተዋጽዖ ማድረግ፣

ለ) አገራዊ የኢንጂነሪንግና ፋብሪኬሽን አቅማችንን በማሳደግና የአምራች ዘርፎች ምርታማነትን፣ ጥራትንና ተወዳዳሪነትን በማጐልበት የኢኮኖሚ

መዋቅራዊ ትራንስፎርሜሽን ማጐልበት፣

ሐ) የሕዝቡን የተደራጀ አቅም በቀጣይነት መገንባትና የልማቱ ባለቤትና ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻል፣

መ) ዴሞክራሲያዊ ልማታዊ መንግስትን በማጠናከር የልማታዊ ፖለቲካል ኢኮኖሚን የበላይነት ማረጋገጥ፣

የዕቅዱ መሠረታዊ አቅጣጫዎች

የሁለተኛው አምስት ዓመት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ መሠረታዊ አቅጣጫዎች በመጀመሪያው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ መሠረታዊ አቅጣጫዎች ላይ የተገነቡ ሲሆን ዕቅዱን የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ለውጥ ማምጣት በሚያስችል መልኩ ለመምራትና ከፍ ብሎ የተቀመጡ ዋና ዋና ዓላማዎችን በቀጣይነት ለማሳካት የሚያስችሉ እና ለዋና ዋና ሴክተሮች ዕቅዶችም እንደመነሻ የሚያገለግሉ ናቸው፡፡ እነዚህ መሠረታዊ አቅጣጫዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡

ሀ) የተጀመረውን ፈጣን፣ ቀጣይና ፍትሐዊ የኢኮኖሚ ዕድገትና ልማት ማስቀጠል፣

ለ) የኢኮኖሚው የማምረት አቅም ላይ ለመድረስ ቅልጥፍና መጨመር እና አምራች ዘርፎችን በማጐልበት በጥራት፣ በምርታማነትና በተወዳዳሪነት የላቀ ዕድገት ማምጣት፣

ሐ) የተፋጠነ የሀገራዊ ባለሃብት ትራንስፎርሜሽን ማምጣትና ብቁ የልማት ኃይል ማድረግ፣

መ) የኮንስትራክሽን ዘርፍ አቅም በማጐልበት የመሠረተ ልማት ተደራሽነትን መጨመርና የአገልግሎቱን ጥራት ማረጋገጥ፣

ሠ) የከተሞችን ፈጣን ዕድገት በአግባቡ በመምራትና በማስተዳደር ለአጠቃላይ ኢኮኖሚው ፈጣን ዕድገት አስተዋፅዖ እንዲጐለብት ማድረግ፣

ረ) የሰው ሃብት ልማትንና የቴክኖሎጅ አቅም ግንባታን ማፋጠንና ዘላቂነቱን ማረጋገጥ፣

ሰ) የመንግሥትን የማስፈፀም አቅም በመገንባት እና የህዝቡን ተሳትፎ በማጐልበት ዲሞክራሲያዊና ልማታዊ መልካም አስተዳደር ማስፈን፣

ሸ) የሴቶችንና የወጣቶችን ብቃት፣ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ማሳደግ እና

ቀ) ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ መገንባት ናቸው።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክም ከመጀመሪያው የሀገሪቱ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ልምድ በመውሰድና የሁለተኛውን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ መሠረት በማድረግ የራሱን የአምሥት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ነድፎ ወደ ሥራ ገብቷል። ባንኩ በዚሁ የአምሥት ዓመቱ ስትራቴጂክ ዕቅድ ዘመኑ ዉስጥ የብር 112.28 ቢሊዮን ብድር ለመፍቀድ፣ የብር 104.34 ቢሊዮን ብድር ለመልቀቅና እና ብር 39.15 ቢሊዮን ከደንበኞቹ ለመሰብሰብ አቅዶ በመሥራት ላይ ይገኛል።

ምንጭ፡ ብሔራዊ የፕላን ኮሚሽን፣ ታህሣሥ 2008 ዓ.ም. እና የ2015/16 የባንኩ ዓመታዊ ሪፖርት

Page 16: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 12

የባንኩ የ50 ዓመት ደንበኛ አቶ እሸቴ ይግዛው የቡላላ ድንቂት እርሻ ንግድ እና ኢንዱስትሪ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ባለቤትና ዋና ሥራ አሥኪያጅ ናቸው። ፕሮጀክቱ በኦሮሚያ ክልል፣ አርሲ ዞን፣ ጀጁ ወረዳ፣ ቀጤ ዶሬ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ከአዲስ አበባ 160 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። የዚህ መጽሔት ዝግጅት ክፍል በኢትዮጵያ ልማት ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የተቋቋሙትን ፕሮጀክቶች ሲጎበኝ እኚህን አንጋፋ የባንኩ ደንበኛ ቃለ መጠይቅ አድርጎ የነበረ ሲሆን “ባንኩ በክፉ እንዲነሳብኝ አልፈልግም” በማለት ለባንኩ ያላቸውን ስሜት ገልጸዋል፤ ዘገባው እንደሚከተለው ተጠናቅሯል።

አቶ እሸቴ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በፊት ገና ወጣት ሳሉ ነበር አባዲሽካ የሚባል በመስኖ የሚለማ ሰፊ እርሻ ላይ ሥራ የጀመሩት። እርሻው በአሁኑ ወቅት በመንግስት እጅ ውስጥ ይገኛል። በወቅቱ የ25 ሺህ ብር ብድር አግኝተው ሥራ እንደጀመሩና በ10 ሺህ ብሩ ዶዘር እንደገዙበት አጫውተውናል፤ የዛሬ ሶስት ዓመት አካባቢ ደግሞ ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለወይን ተክል ልማት የ23 ሚሊዮን ብር ብድር ተጠቃሚ ሆነዋል።

አዛውንቱ ባለሃብት በእጆቻቸው እያመለከቱ “ይህ የምታዩት የወይን እርሻ ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ በተገኘው ብድር የተጀመረ እርሻ ነው። እንግዲህ የእርሻው ሆኔታ በምታዩት ደረጃ ላይ ነው የሚገኘው (በወቅቱ ያበበ ነበር)። የወይን ምርት በሚሰበሰብበት ጊዜ እና በሌሎች ወቅታዊ ሥራዎች ወቅት ከ350 በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ማኅበረሰብ አባላት የሥራ ዕድል ይፈጠራል፤ የወይን መትከል መርኃ ግብሩ እንደተጠናቀቀም ምርቱን ወደ ኢንዱስትሪ በመለወጥ የወይን ጠጅ ፋብሪካ በእዚሁ የእርሻ ቦታ ላይ ማቋቋም ነው ዓላማችን” ብለዋል።

ከባንኩ ጋር ስላላቸው የግማሽ ምዕተ ዓመት ትውውቅ ሲገልጹ ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ጋር እናንተ ሳትወለዱ በፊት ነው ሥራ የጀመርኩት። በጊዜው የነበሩት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ዋና ስራ አስኪያጅ (በአሁኑ ስያሜ ፕሬዝዳንት) ክቡር አቶ ወርቁ ሀብተወልድ እና ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሙሉጌታ ገ/ወልድ እርሻዬን ጎበኙ። እርሻውም የጥጥ እና የአትክልት እርሻ ነበር። በጊዜው የመስኖ እርሻ ከጀመሩት ኢትዮጵያውያን ውስጥ አንዱ ነበርኩ:: ከጉብኝቱ በኋላ ሁሉም ነገር ጥሩ ስለነበር ብድሩ ተፈቀደ። ከብድሩ መፈቀድ በኋላ በጊዜው በነበረው ፖሊሲ መሠረት የሚሰጠው ብድር የከተማ ቦታ ያለው ወይም ዋስትና ማስያዝ የሚችል ነበር። ሆኖም እኔ በጊዜው ምንም የማስይዘው ነገር አልነበረኝም:: ይህ ሁኔታ ሁለቱም የሥራ ኃላፊዎች አስደነገጠ። ብድሩን እንዳላገኝ ወዲህ የፖሊሲ ችግር አለ፤ እንዳልከለከል ደግሞ በስራው በጣም ተደስተዋል፤ አምነውበታልም። በወጣትነት ዘመኔ ደግሞ እዚህ በርሃ ውስጥ ገብቼ መስራቴንም አድንቀዋል። ስለዚህ በሥራ አስኪያጆቹ ኃላፊነትና ዋስትና የብድሩን መጠን በተወሰነ ደረጃ በመቀነስ እንዲሰጠኝ እንጂ

መከልከል እንደሌለበት ታምኖበት ተፈቀደልኝና የሥራዬን መጀመሪያ “ሀ” ብዬ ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ጋር ጀመርኩ ብለዋል። የብድሩን መጠን ሲናገሩ በመጀመሪያው ዙር ወደ 25 ሺህ ብር አካባቢ እንደነበርና በጊዜ ሂደት እያደገ መጥቶ ወደ 50 ሺህ ብር ከፍ ማለቱን ገልጸዋል።

አቶ እሸቴ በመቀጠል በብዙ ድካምና ልፋት የተቋቋመው አባዲሽካ እርሻ ትልቅ ደረጃ ከደረሰ በኋላ በደርግ ተወረሰ። እኔም እርሻው ከተወረሰ በኋላ ተመልሼ እንደገና እጅና እግሬን አጣጥፌ መቀመጥ ሆነ። ምንም ስራ የለም። ሆኖም ከ10 ዓመት በኋላ እንደገና ተመልሼ ሥራ ከምፈታ አንዳንድ ነገሮችን ላጥና አልኩና ወደ ኢትዮጵያ ልማት ባንክ ስሄድ በአጋጣሚ ከአንድ የውጭ አገር ዜጋ ከሆኑት ሲኞር ቫላንቲ እና ባለቤታቸው ወ/ሮ ማርያ ከሚባሉ የጣልያን ዜጎች ጋር ተገናኘሁ። እነርሱም የእንጨት መሰንጠቂያ ፋብሪካ ነበራቸውና ከእኛ ጋር አብረህ ብትሰራ ብለውኝ በወቅቱ እኔ ምንም ገንዘብ ስሌለኝ ልማት ባንክ ሄጄ አማከርኩ። በወቅቱ የነበሩት የባንኩ ኃላፊዎችም የድሮ ታሪኬን በማየት እና አሁን ያለሁበትን ሁኔታ በመመልከት የእንጨት መሰንጠቂያ ጅማ አጋሮ ላይ እንዳቋቁም በጊዜው የነበረው የሶሻሊዝም ሥርዓት የሚፈቀደው ካፒታል መጠን ከ500ሺህ ብር የበለጠ ባለመሆኑ ይህኑን ያህል ብር ያለምንም ዋስትና ለመሰንጠቂያው ብቻ ተፈቅዶልኝ የእንጨት መሰንጠቂያ ፋብሪካ አቋቁሜ እየሰራሁ ልጆቼንም ውጭ አገር ድረስ በመላክ አስተምሬ ለቁም ነገር አብቅቻለሁ፤ ይህም ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ በየተገኘው ብድር በተሰራ ሥራ ነው።

አቶ እሸቴ “እንደው በእውነት ለመግለጽ በሚያቅት ደረጃ የሥራዬ ሁሉ መሰረት ነው፤ ለእኔ ብቻ ሳይሆን ለባንኩ ደንበኞች ትልቅ አገልግሎት የሚሰጥና በብድር የሚደግፍ ጥሩ ባንክ ነው:: አሉ ከሚባሉ አንጋፋ ባንኮች ውስጥ ልማትን የሚደግፍ ታሪክ ያለው ባንክ ነው። እኔ በእድሜዬ ያየሁት ነገር ባንኩ በትክክል ለሚሰሩ ሰዎች ሁሉ ድጋፍ ሰጪ መሆኑን ነው። ነገር ግን ትልቁ ችግር ባለመተማመን ወደ ፕሮጀክት ሥራ በሚገቡና በእርሻውም ሆነ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ባልተስተካከለ መንገድ መሄድ ነው። ከዚህ ውጭ በእውነት ከልማት ባንክ ጋር በትክክል ከተሰራ የክፍያ ጊዜ እንኳ ቢያቅተን የጊዜ ገደቡን በማስረዘም ሰዎችን የሚደግፍ ነው:: በተለይም ለባንኩ ታማኝ ከሆኑና ዕዳቸውን በትክክል ከከፈሉ፣ ልማታቸውን በትክክል ካካሄዱ፣ ባንኩ ምንጊዜም እገዛ የሚያደርግላቸው ስለሆነ ወደ ባንኩ እንዲመጡ እመክራለሁ” በማለት አብራርተዋል።

ባለሃብቱ እንደ ችግር ያነሱት ባንኩ የሚሰሩትንና የማይሰሩትን ሰዎች መለየት አለመቻሉ ነው። በማይሰሩ ሰዎች ምክንያት የሚሰሩ ሰዎች ሥራቸው ይደናቀፋል። ስለዚህም ባንኩ የሚሰሩና የማይሰሩ ሰዎችን መለየት ይኖርበታል ብለዋል።

“እንግዲህ አሁን የምታዩት እርሻ በጣም አረንጓዴ ሆኖ ነው የምታዩት። ልክ እንደዚሁ ይህን አረንጓዴ የወይን እርሻ ስታይ አንተም ውስጥህ እንዲሁ ይለመልማል። እንዲሁም በሌላ በኩል በበሽታዎች ወይም በአየር ፀባይ አለመስማማት ይህ እርሻ ሊበላሽ ሊከስም ይችላል፤ ያን ጊዜም እንዲሁ አንተም ትጠወልጋለህ፤ ትደርቃለህ፤ ተስፋ ትቆርጣለህ። ምን ለማለት ፈልጌ ነው የእርሻ ስራ ፕሮግራም ከሌለህ፣

ከደንበኞች ድምጽ

መግቢያየኢትዮጵያ ልማት ባንክ ረጅም ዕድሜ ያለው አንጋፋ የፋይናንስ ተቋም ሲሆን በአገሪቱ ውስጥ የሚካሄዱ የልማት ፕሮጀክቶችን በፋይናንስና በቴክኒክ እየደገፈ ቆይቷል፤ አሁንም ከዚህ ቀደም ከነበረው በተሻለ መልኩ በመደገፍ ላይ ይገኛል። በዚሁ መሠረት ባንኩ በሁሉም የአገሪቱ ክልሎች በገንዘብና በቴክኒክ እየደገፋቸው ከሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል የሁለት ፕሮጀክቶችን አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴና አፈጻጸም ምን እንደሚመስል እንደሚከተለው ተጠናቅሮ ቀርቧል።

መልካም ንባብ!

የ82 ዓመቱ አዛውንት ባለሃብት

“ባንኩ በክፉ እንዲነሳብኝ አልፈልግም”

Page 17: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 13

በእቅድ ካልተጓዝክ፣ የረጅም ጊዜ እቅድ ካላስቀመጥክ በሚያጋጥመው ችግር ምክንያት ቶሎ የምትደነግጥ ከሆነ የእርሻ ስራ በአንድ ጊዜ /በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ/ የምታቆምበት ደረጃ ትደርሳለህ። ስለዚህ ትልቁ ችግራችን የባንኩ ብድር ሁልጊዜ የተመቻቸ ላይሆን ይችላል። ስለዚህ በዚህም ምክንያት ያለንን ንብረት እንሸጣለን። ከሌላ እየተበደርን የእርሻ ልማቱን እናስኬዳለን። ይህ ብቻ አይደለም የገበያውም ችግር ያጋጥማል። ስለዚህ ጠንክሮ መሥራት ያስፈልጋል” በማለት ተናግረዋል።

በሥራ ዘመናቸው ያዘኑበትን ጊዜ ሲናገሩ “ከፍተኛ ችግር ገጠመኝ የምለው ብዙ ውጣውረዶችን አሳልፌ በመጨረሻ በደርግ ዘመን ንብረቴ /እርሻዬ/ የተወረሰ ግዜ ነበር ። በዚህን ጊዜ መቋቋም የማልችለው ችግር ውስጥ ገብቼ ነበር። እንኳን ስራ ልሰራ የምመገበው እስከማጣት እና ልጆቼንም ማስተማር እስኪያቅተኝ ድረስ ችግር ውስጥ ገብቼ ነበር። አሁን ግን እግዚአብሔር ይመስገን የሰባት ልጆች አባት ነኝ፤ አምስት ሴት እና ሁለት ወንድ ልጆች አሉኝ፤ ሴቶች ልጆቼ በጣም ጠንካሮች ናቸው። ከጠንካሮቹ መሀል አንዷና የዚህ ድርጅት ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ወ/ሪት ኤልሳቤት እሸቴ ትባላለች፤ የእርሻውም ሆነ የሁሉም ሥራ ሞራል ሰጭና ጠንካራ ልጅ ናት” በማለት አሞካሽተዋታል።

በመቀጠል የዝግጅት ክፍሉ ከሥራው ተረካቢና ከድርጅቱ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ወይዘሪት ኤልሳቤጥ እሸቴ ጋር ቆይታ አድርጓል። ምክትል ሥራ አስኪያጇ በእርሻ ሥራ ላይ ከ10 ዓመት በላይ የሰራች መሆኗንና በትምህርት ደረጃ በቢዝነስ ማኔጅመንት ዲፕሎማ፣ በኢኮኖሚክስ የመጀመሪያ ዲግሪ ያጠናቀቀች ሲሆን የሁለተኛ ዲግሪዋን ደግሞ በመማር ላይ እንደምትገኝ ነግራናለች።

ወ/ሪት ኤልሳቤጥ “ድርጅቱ በቤተሰብ የተመሠረተ ድርጅት ነው፤ የድርጅቱም አመሰራረት በእርሻ ልማት ላይ የተመሰረተ ሆኖ ከእርሻ ክፍል ውስጥ ይህ የወይን እርሻ አንዱ ነው” ብላናለች።

በመቀጠል የወይን እርሻው ከመንግሥት በተሰጠ 80 ሄክታር የሊዝ መሬት ላይ የተመሰረተ መሆኑን፣ ፕሮጀክቱ በግል በድርጅቱ መዋጮ ተነስቶ ስራውን ለማስፋፋት ከሚያደርገው ሂደት ውስጥ የባንክ ብድር አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ለእርሻው በተዘጋጀ የአዋጭነት ጥናት መሰረት ለባንኩ መቅረቡን፣ ባንኩም በቀረበው ጥናት ላይ አንዳንድ ማሻሻያዎችና ማስተካከያዎች እንዲያደርጉ በሰጠው አስተያየት መሰረት አስተካክለው ማቅረባቸውን፣ ባንኩም ወደ 23 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ብድር በመስጠት ከድርጅቱ መዋጮ ወደ ብር 46 ሚሊዮን አድርገው በአዲስ ቴክኖሎጂ ወደ እርሻ ሥራ መግባታቸውን ገልጻለች።

ምክትል ሥራ አስኪያጇ ስትናገር የወይን እርሻ በሀገራችን

ብዙ የተለመደ አይደለም፤ በአፍሪካ እንደ ግብጽ፣ ደቡብ አፍሪካ እና በተወሰኑ ሀገራት ውስጥ ብቻ የሚመረት ነው። የወይን እርሻ ኢትዮጵያ ውስጥ አዋጭነቱ ምንድ ነው ተብሎ ሲታይ የአየር ፀባዩ እና የአፈሩ ተስማሚነት አመቺ ሆኖ መገኘት በዓመት ሁለት ጊዜ ማምረት የሚያስችል መሆኑ ብቻ ራሱ ትርፋማ መሆን እንደሚቻል ያሳያል ።

የወይን እርሻው በዓመት ሁለት ጊዜ ምርት ይሰበሰባል፤ የሰባት ወር ማረፊያ ጊዜ እየተሰጠው እየተገረዘ እንደገና ምርት ይሰጣል፤ ለ36 ዓመታት የሚቆይ ተክል ነው፤ የግብርና አግሮኖሚው እንዳለ ሆኖ በወይን ላይ አብዛኛው ስራ ወደ ኢንጂነሪንግ ፓርቱ ያደላል፤ ወይኑ የሚቆምበት የሚዘረጋበት ሜንቴን የሚደረግበት እነዚህ ደግሞ ወጪያቸው ከፍተኛ ነው፤ ያንን ለመሸፈን ባደረግነው ጥረት ባንኩ በሰጠን ብድር ስራውን ሙሉ በሙሉ ለመስራት የሚያስችል ሂደታችንን ጀምረናል።

የዲሪፕ ኢሪጌሽን ሲስተም እዚህ ውስጥ መኖር አለበት አከባቢያችን ትንሽ ለወጥ ያለ ነው አዋሽ አፈራማ ወንዝ ነው። አፈራማ በመሆኑ ንፁህ ውሃ አግኝተን ከመጠቀም አኳያ የዲሪፕ ኢሪጌሽን ሲስተም ማቋቋም ስለነበረብን ትንሽ ወጪና ከበድ ያለ በጀት የሚያስፈልጋቸው ችግሮች ቢያጋጥሙንም ችግሮችን ለመፍታት ጠንካራ አቋም ስለነበረን ችግሮቻችንን ለመፍታት ችለናል። በዚህም መሰረት የዲሪፕ ኢሪጌሽን ሲስተሙ ተዘርግቶ የቋሚ እንጨቱ ሽቦዎቹ ተማልተው ስራውን ማስኬድ ችለናል። አሁንም ቢሆን ትልቁ ችግራችን የመብራት እጥረት ነው፤ ይህም ስራችንን ከፕሮግራም ውጭ እንድናካሂድ አስገደደን፤ በተወሰኑ ስራዎች ላይ እንደውም ቀደም ብለን በማምረት ለገበያ እያቀረብን ነው። እንዲሁም በገበያ ላይ ጥሩ ምርት በማቅረብ ተወዳዳሪ ለመሆን ዓላማ አለን ነገር ግን አሁን ላይ ምርታችንን ተጠቃሚ ለሆኑት አዋሽ ወይን ጠጅ ፋብሪካና ለካስቴል ዋይነሪ በመሸጥ ላይ እንገኛለን፤ በሄክታር ከ200 እስከ 400 ኩንታል እያመረትን እንገኛለን፤ እንዲሁም የወይኑ እርሻ እድሜ በጨመረ ቁጥር የማምረት አቅሙ ከፍ እያለ ነው የሚመጣው ብላለች።

ሥራው ፕሮፌሽናል በሆኑ ሰዎች መሠራት አለበት፤ በአገራችን በዘርፉ የተማረና የሰለጠነ የሰው ኃይል ዉስን ነው፤ ይህም ቢሆን የአግሮኖሚ ባለሙያ የሆኑትን በማሳተፍ ነው ይህን ስራ የምንስራው። በዚህም ድርጅቱ 20 ቋሚ ሠራተኞች ያሉት ሲሆን ምርት በሚሰበሰብበት ጊዜ ደግሞ 350 የሚደርሱ ሠራተኞችን በኮንትራት ቀጥረን እናሰራለን፤ ከዚህ ውስጥ የሴቶቹ ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ በማደግ ላይ ይገኛል በማለት ገልጸዋል።

ለወደፊቱ የገበታ ወይኖችን ወደ ውጭ ለመላክ ዕቅድ የለንም ሆኖም በቱሪዝም ኢንዱስትሪ ውስጥ ገብተን በትናንሽ ጠርሙሶች በማሸግ ከውጭ ለሚመጣው ቱሪስት ለሳምፕል እንዲገዛው የማዘጋጀት እና ከቱሪዝም ጋር የተያያዘ ኢንቫይሮመንት የመፍጠር ዕቅድ ነው ያለን ብላለች።

ድርጅቱ ለአካባቢው ኅበረተሰብ እያበረከተ የሚገኘውን አስተዋጽኦ በሚመለከት ስትገልጽ ይህ አካባቢ ቆላማ ነው። ስለዚህም ኑሮውን ለመደጎም የሚረዳው ድርጅት ነው። ከድርጅታችን በሚያገኘው ገቢም ደስተኛ ነው። አከባቢው በርሃማ እንደመሆኑ መጠን እርሻችን ለአካባቢው ጠቃሚ ነው። ምንም ዓይነት አደገኛ ኬሚካል አንጠቀምም። እንደውም ቅጠሉ ለአፈሩ እንደማደበሪያነት ያገለግላል ብላለች።

ወላጆቿን በሚመለከት “ከአባታችን ጠንካራነትን ተምሬያለሁ፤ በግብርና ስራ መኩራት እንዳለብኝ አስተምሮኛል። ከእናታችንም እንዲሁ ጠቃሚ ትምህርት ወስጃለሁ፤ እናታችን የከብት እርባታ ነበራት፤ ሥራው አድካሚ ነው፤ በዚያ ላይ አሉታዊ አስተያየቶች ይሰማሉ፤ ሆኖም በእነርሱ ጥንካሬ እበረታለሁ፤ ለዚህም አመሰግናቸዋለሁ” በማለት ሀሳቧን ደምድማለች።

አቶ እ

ሸቴ ይ

ግዛው፣ የድ

ርጅቱ ስ

ራ አ

ስኪያጅ

Page 18: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 14

ዜ.ል.ባ.፡- በመጀመሪያ ራስዎን ቢያስተዋውቁን፡፡

ኢንጂነር ሰሎሞን፡- ኢንጂነር ሰሎሞን ደስታ እባላለሁ፡፡ የሰማያታ እምነበረድ ፋብሪካ ዋና ሥራ አስኪያጅ ነኝ፡፡

ዜ.ል.ባ.፡- ሰማያታ እምነበረድ ፋብሪካ ከተቋቋመ ምን ያህል ጊዜ ሆነው@ በምን ያህል ካፒታል ተቋቋመ?

ኢንጂነር ሰሎሞን፡- ፋብሪካው ከተቋቋመ ሁለት ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡ የተቋቋመበት ካፒታልም 400 ሚሊዮን ብር ነበር፡፡

ዜ.ል.ባ.፡- ለፋብሪካችሁ የምትጠቀሟቸውን ግብዓቶች (ጥሬ ዕቃዎች) ከየት ነው የምታገኙት?

ኢንጂነር ሰሎሞን፡- ከ95% በላይ የሚሆነውን የጥሬ እቃ አቅርቦት ከሃገር ውስጥ ነው የምናገኘው፡፡ ይህም የውጭ ምንዛሪን ከማስቀረት አንፃር ትልቅ አስተዋፅኦ አለው፡፡

ዜ.ል.ባ.፡- ከውጭም ሆነ ከሀገር ውስጥ ገበያ ጋር ያላችሁ ትስስር ምን ይመስላል?

ኢንጂነር ሰሎሞን፡- በዕቅድ ደረጃ ለውጭ ሃገር ገበያ ለማቅረብ አቅደናል፡፡ በዋናነት ግን በተቻለ አቅም ከውጭ የሚገቡትን የእምነበረድ ዓይነቶች በሃገር ውስጥ በሚመረተው በመተካት የውጭ ምንዛሪን ለሃገር የማስቀረት ስራ ለመስራት ቅድሚያ እንሰጣለን፡፡ የተለየ ምርት በመያዝ በዓለምአቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የመሆን ራዕይን ይዘን በመንቀሳቀስ ላይ እንገኛለን፡፡

ዜ.ል.ባ.፡- የዚህ ፋብሪካ መቋቋም ለምን ያህል ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥሯል?

ኢንጂነር ሰሎሞን፡- ፋብሪካው ለ150 ቋሚ እና 150 ጊዜያዊ ሠራተኞች የሥራ ዕድል ፈጥሯል፡፡ በተጨማሪም በቅርቡ የምንጀምራቸው አዳዲስ ስራዎች ስላሉ የሰራተኞቻችንን ቁጥር በእጥፍ ለማሳደግ ያስችለናል፡፡

ዜ.ል.ባ.፡- ማህበራዊ ግዴታን ከመወጣት አንፃር ፋብሪካችሁ ምን ሰርቷል?

ኢንጂነር ሰሎሞን፡- የፋብሪካችንን ማኅበራዊ ግዴታ (Social Responsibility) ለመወጣት በጤና ዘርፍና በሌሎች የልማት ስራዎች ላይ እንሳተፋለን፡፡ እንዲሁም በአካባቢው ላይ ችግር የነበረውን የአፈር መሸርሸር ለመከላከል የሚያስችል ሥራ መሬት ላይ ሰርተናል፡፡ ይህ እንደ ጀማሪነታችን እየሰራነው ያለ ነገር ነው፡፡ ለወደፊት ግን የከተማዋንም ሆነ የአካባቢውን ልማት ለማገዝ በሚደረጉ ስራዎች ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ ነን፡፡

ዜ.ል.ባ.፡- የዕውቀት ሽግግር ከማድረግ አንፃር ከዩኒቨርስቲዎች ወይም ከሌሌሎች ተቋማት ጋር የመስራት ልምድ አላችሁ?

ኢንጂነር ሰሎሞን፡- እዚህ ካሉ የቴክኒክ ትምህርት ቤቶች ጋር ለመስራት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመናል፡፡ እንደ ኢትዮጵያ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ME-TEC) ካሉ ወርክሾፕ ካላቸው ተቋማት ጋር እንዲሁም

ከመቀሌ ዩኒቨርስቲ የተለያዩ የምርምር ስራዎችን ከሚሰሩ ዩኒቨርስቲዎች ጋር በጋራ ለመስራትም አቅደናል፡፡

ዜ.ል.ባ.፡- የፋብሪካው ተረፈ ምርቶች የአካባቢ ብክለት እንዳያስከትሉ ከመከላከል አንፃር ምን እየሰራችሁ ነው?

ኢንጂነር ሰሎሞን፡- የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል በዋናነት እየሰራን የምንገኘው የእምነበረዱን ድንጋይ በውሃ የሚቆርጥ ማሽን መትከላችን ነው፡፡ ብዙ ኬሚካል አንጠቀምም፡፡ ውሃውንም እየመላለስን (Recycle) እያደረግን ነው የምንጠቀመው፡፡ ስለሆም የተበከለ ውሃ ከፋብሪካችን አይወጣም፡፡ ሁሉም ተረፈ ምርቶች ተመልሰው ለሌላ ሥራ አገልግሎት ስለሚውሉ ከፋብሪካችን የሚወጣ አካባቢን የሚበክል ነገር አይኖርም፡፡ በዚህ በኩል ጥሩ ነገር እያደረግን ነው ብዬ አምናለሁ፡፡

ዜ.ል.ባ.፡- የኢትዮጵያ ልማት ባንክን አስተዋጽኦ እንዴት ያዩታል?

ኢንጂነር ሰሎሞን፡- የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለፋብሪካችን መቋቋም ያደረገው አስተዋጽኦ እጅግ መሠረታዊ የሚባል ነው፡፡ ከገንዘብ ብድር ባሻገር የቴክኒክ ድጋፍ፣ የአጠቃላይ ክትትል እና የፋብሪካው ማሽነሪዎች በተቀላጠፈ ሁኔታ ወደ ሃገር ውስጥ እንዲገቡ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል፡፡ ባጠቃላይ ልማት ባንክ ባይኖር ይህ ፋብሪካ ይኖራል የሚል እምነት የለኝም፡፡ ምክንያቱም ከምሥረታው ጀምሮ እስካሁን ድረስ ትልቅ ድጋፍ ነው ያደረጉልን፡፡

ይህ ፋብሪካ ለብዙ ሰዎች የስራ እድል ፈጥሯል፡፡ ለዚህ ደግሞ የባንኩ አስተዋፅኦ አለበት፡፡ በሃገርም በክልልም ደረጃ ቢታይ ፋብሪካው ትልቅ የልማት አጋር ነው ለማለት ይቻላል፡፡ ለሌሎችም ማሳያ ስለሚሆን ወደማኑፋክቸሪንግ ስራ ለመግባት ለሚያስቡ ትልቅ ማበረታቻ ሊሆን ይችላል፡፡ ስለዚህ ልማት ባንክ ድጋፉን ከቀጠለ ሌሎች ተመሳሳይ ፋብሪካዎችም እንዲቋቋሙ መንገድ ይከፍታል ብዬ አስባለሁ፡፡

ዜ.ል.ባ.፡- የወደፊት ዕቅዳችሁ ምንድነው?

ኢንጂነር ሰሎሞን፡- ራዕያችን በግራናይት ምርት በአፍሪካ

በዚህ አምድ ሥር በትግራይ ክልል ዉቅሮ ከተማ በኢትዮጵያ ልማት ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የተቋቋቀመውን እምነበረድ ፋብሪካ በማስመልከት የመጽሔት ዝግጅት ክፍሉ ከድርጅቱ ሥራ ኃላፊና ሠራተኞች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጎ እንደሚከተለው አቅርቧል።

ሰማያታ እምነበረድ ፋብሪካ

ከደንበኞች ድምጽ

Page 19: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 15

ቀንድ ግዙፍ አምራች ኩባንያ ለመሆን ነው፡፡ አዳዲስ የግራናይት ምርቶችን ለማምረት በጥናት ላይ እንገኛለን፡፡ ጥናቱ እንዳለቀ ወደ ማምረት እንሸጋገራለን፡፡ ነጭ፣ ጥቁር እና ፒንክ የመሳሰሉት አዳዲስ የእምነበረድ ምርቶች አሉን፡፡ እነዚህ ወደ ዓለም ገበያ የምንገባባቸው ምርቶች ናቸው፡፡ እነዚህን በማምረት የምስራቅ አፍሪካውን ገበያ መቆጣጠር ነው ዓላማችን፡፡ እንደምናሳካውም ጅምራችን ምስክር ነው፡፡

ዜ.ል.ባ.፡- በመጨረሻ ማስተላለፍ የሚፈልጉት መልዕክት ካለ?

ኢንጂነር ሰሎሞን፡- የመጨረሻ መልዕክቴ ለኢትዮጵያ ልማት ባንክ ነው። ባንኩ ትልቅ ድጋፍ ነው ያደረገልን። ገንዘቡን በጊዜ በመልቀቅና አስፈላጊውን የቴክኒክ ድጋፍ በማድረግ የቅርብ ክትትል በማድረግ ብዙ አስተዋፅኦ አድርጎልናል፡፡ ያ ለኛ ጥንካሬ ነው የሆነን፡፡ ለወደፊቱም ይህ ድጋፍና ክትትል እንዲቀጥልልን እና ለጥያቄዎቻችን ፈጣን ምላሽ እንዲሰጠን አደራ ማለት እወዳለሁ፡፡ እስከዛሬ ላደረገልን ድጋፍ በድርጅቱ ስም በጣም እናመሰግናለን፡፡

ሊሊ አብርሃ (ኦፕሬተር)

ዜ.ል.ባ.፡- ስምሽንና የሥራ ድርሻሽን በመተዋወቅ እንጀምር፡፡

ሊሊ አብርሃ፡- ሊሊ አብርሃ እባላለሁ፡፡ ኦፕሬተር ነኝ፡፡

ዜ.ል.ባ.፡- ስራ ከጀመርሽ ምን ያህል ጊዜ ሆነሽ?

ሊሊ አብርሃ፡- 7 ወር አካባቢ ሆኖኛል፡፡

ዜ.ል.ባ.፡- እዚህ ፋብሪካ ውስጥ በመስራትሽ አገኘሁ የምትይው ጥቅም ምንድነው?

ሊሊ አብርሃ፡- አዲስ ፋብሪካ በመሆኑና ሁሉም ነገር ለኔ አዲስ በመሆኑ ስራውን እንድወደው አድርጎኛል፡፡ ራሴን የማስተዳድርበት ገቢ እንዳገኝ ስላደረገኝም ጠቅሞኛል፡፡

ዜ.ል.ባ.፡- የዚህ ፋብሪካ በዚህ አካባቢ መከፈት ለወጣቶች የስራ እድል ከመፍጠር አንፃር የሚያበረክተውን አስተዋፅኦ እንዴት ታይዋለሽ?

ሊሊ አብርሃ፡- በጣም ትልቅ ጥቅም ነው ያለው 10ኛ ክፍል ተፈትነው ውጤት ሳይመጣላቸው ቀርቶ ስራ አጥ ሆነው የነበሩ ብዙ ወጣቶች ነበሩ፡፡ አሁን በዚህ ፋብሪካ ውስጥ ስራ በመጀመራቸው ራሳቸውንም ሆነ ቤተሰባቸውን መርዳት ጀምረዋል፡፡ ይህ በራሱ ትልቅ አስተዋፅኦ ነው፡፡ ከዚህ አካባቢ ተነስተው በሌላ ሃገር ስራ ፍለጋ ለሚሄዱ ወጣቶችም

ከአካባቢያቸው ሳይርቁ እንዲሰሩ ከማድረግ አንፃር ትልቅ አስተዋፅኦ ነው ያለው፡፡

ነቢያት በዳሶ (የምርት ክፍል ኃላፊ)

ዜ.ል.ባ.፡- ስምህንና የሥራ ኃላፊነትህን አስተዋውቀን፡፡

ነቢያት፡- ነቢያት በዳሶ እባላለሁ፡፡ የፋብሪካው ምርት ክፍል ኃላፊ ነኝ፡፡

ዜ.ል.ባ.፡- ከተቀጠርክ ምን ያህል ጊዜ ሆነህ?

ነቢያት፡- አንድ ዓመት ከ6 ወር ሆኖኛል፡፡ ያው ፋብሪካው ተቋቁሞ ሥራ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ነበርኩ፡፡

ዜ.ል.ባ.፡- እዚህ ፋብሪካ ውስጥ በመስራትህ አገኘሁ የምትለው ጥቅም ምንድነው?

ነቢያት፡- ከፋብሪካው አገኘሁት የምለው ጥቅም ማሽኖቻችን በጣም ዘመናዊ ናቸው፡፡ ብዙ እውቀት ለማግኘት እና ከቴክኖሎጂው እኩል ለመራመድ አስችሎናል፡፡ ራሴንና ቤተሰቤን የምረዳበት ገቢ እንዲኖረኝ አድርጎኛል፡፡

ዜ.ል.ባ.፡- የዚህ ፋብሪካ በዚህ አካባቢ መከፈት ለወጣቶች የስራ እድል ከመፍጠር አንፃር የሚያበረክተውን አስተዋፅኦ እንዴት ታየዋለህ?

ነቢያት፡- የፋብሪካው መከፈት አስተዋፅኦ በጣም ትልቅና ዘርፈ ብዙ ነው፡፡ በዚህ አካባቢ ይህ ፋብሪካ መከፈቱ በራሱ እንደ ሀገርም እንደ ከተማም ትልቅ አስተዋጽኦ ነው ያለው፡፡ ከዋና ዋና ባለሙያዎች በተጨማሪ ከ250 በላይ የሚሆኑ ስራ አጥ የነበሩ ወጣቶችን ተጠቃሚ አድርጓል፡፡ በአጠቃላይ የስራ እድል ከመፍጠርና ወጣቶችን ተጠቃሚ ከማድረግ አንፃር ትልቅ ስራ እየሰራ የሚገኝ ፋብሪካ ነው፡፡

ዜ.ል.ባ.፡- በፋብሪካው ውስጥ የልማት ባንክ አስተዋፅኦን እንዴት ታየዋለህ?

ነቢያት፡- ባለኝ መረጃ መሠረት ለዚህ ፋብሪካ መከፈት የልማት ባንክ አስተዋፅኦ ቀላል የሚባል አይደለም፡፡ እነዚህ ማሽኖች ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ትልቅ እገዛ ነው ያደረገልን፡፡ በርካታ የቴክኒክ ድጋፎችን አድርጓል፡፡ ወደፊትም የማርብል ፋብሪካችንን ስናቋቁም የተለመደ ድጋፉን እንዲያደርግልን አደራ እንላለን፡፡

Page 20: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et

ከስራ ክፍሎቻችን

16

የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት ለአገራችንም ሆነ ለኢትዮጵያ ልማት ባንክ አዲስ ሥራ ነው። ይህን ተልዕኮ መንግሥት ለባንኩ ከሰጠው እ.አ.አ. ከጃንዋሪ 1 ቀን 2016 ጀምሮ መጠነ ሰፊ የሆነ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ሲያከናውን ቆይቶ ወደ ሥራ ገብቷል። በዚሁ መሠረት የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት ለመስጠት የነበሩ ቅድመ ዝግጅቶች፣ ወደ ሥራ ሲገባ የነበሩ አስቻይ ሁኔታዎችና ተግዳሮቶች ምን እንደሚመስሉና የተወሰዱና እየተወሰዱ የሚገኙ የመፍትሔ ሃሳቦችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ምን እንደሆኑ በባንኩ የሊዝ ፋይናንሲንግ ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ተሾመ አለማየሁ አብራርተው ነግረውናል።

መልካም ቆይታ!

ዜልባ፡- የሊዝ ፋይናንስ ጽንሰ ሀሳብ ምንድነው?

አቶ ተሾመ፡- የሊዝ ፋይናንስ ጽንሰ ሃሳብ በዓይነት ፋይናንስ የማድረግ የባንክ አገልግሎት ነው። በተለይም በውጭው ዓለም በስፋት ሲሰራበት የነበረ አገልግሎት ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ነው ወደ አገራችን የመጣው። እንግዲህ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እንደሚታወቀው ፕሮጀክቶችን በገንዘብ ሲደግፍ ነው የሚታወቀው። ነገር ግን አዲሱ አገልግሎት ወይም ሊዝ ፋይናንሲንግ በዓይነት (Capital Goods) የማምረቻ መሣሪያዎችን ማቅረብ ማለት ነው። የተለያየ ዓይነት የሊዝ ፋይናንሲንግ ሞዳሊቲዎች አሉ። የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ይህን አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው በዱቤ ግዥሥርዓት (Hire-Pur-chase Modality) መሠረት ነው ። ጠቅለል ባለ መልኩ ገና በጅምር ላይ የሚገኝ እየተሰራበት ያለ አዲስ ፕሮዳክት ነው ማለት ይቻላል። በእኛ አገር እንዲሁም በባንኩ ታሪክ አዲስ ቢሆንም በውጭው ዓለም ግን በስፋት እየተሰራበት የሚገኝ አገልግሎት ነው። ይህም በዓለም ላይ ረጅም ዕድሜ ያስቆጠረ አገልግሎት መሆኑን ነው መናገር የሚቻለው።

ዜልባ፡- ይህ ሥራ በምን መስፈርት ነው ለባንኩ የተሰጠው?

አቶ ተሾመ፡- በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ገንዘብ የመበደር ዕድል (Financial Access) እንዲኖራቸው መንግስት ወስኗል። እነዚህንም ማሳደግና ለኢኮኖሚው አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ በተለይም ደግሞ ከእርሻ ወደ ኢንዱስትራላይዜሽን በሚደረገው የስትራክቸራል ትራንስፎርሜሽን ላይ እንዲሁ አስተዋኦ እንዲያደርጉና የሥራ ዕድል እንዲፈጥሩ መንግስት ይህንን ከግምት ውስጥ በማስገባት ይህ አገልግሎት ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ተደራሽ መሆን እንዳለበት አምኗል። በዚሁ የዕቅድ ዘመን አካትቶ ነው የሚገኘው። ይህን ተልዕኮ ከመወጣት አንጻር የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የመንግሥት ፖሊሲ አስፈጻሚ ባንክ ነው። ስለሆነም በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ላይ የተቀመጡ ፕሮጀክቶችን ፋይናንስ ከማድረግ አንጻር ከመንግሥት ከፍተኛ ኃላፊነት የተሰጠው ባንክ ነው። ስለዚህ ከሌሎች ባንኮች በተሻለ በዚህ በማይክሮ ኢንተርፕራዝ ፋይናንሲንግ እንዲሁም በፕሮጀክት ፋይናንሲንግ የረጅም ጊዜ ልምድ ስላለው የዲስትሪክቶችንና የቅርንጫፎቹን ብዛት በማስፋት ይህንን አገልግሎት ለመስጠት የተሻለ ባንክ ሆኖ የተገኘው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ነው። ስለሆነም መንግሥት የሊዝ ፋይናንስ ፕሮግራም ተግባራዊ እንዲደረግ ሲወስን ለባንኩ ይህ ተልዕኮ ተሰጥቶታል። በሌላም በኩል የባንኩ ካፒታል እንዲያድግ የተደረገበት ሁኔታ አለ። ስለዚህም ቀደም ብሎ ከተሰጠው ተልዕኮ፣ የመዋቅር ሥራ ከመሠራቱ እንዲሁም ብዙ ቅርንጫፎች እንዲኖሩት ከመደረጉ በተጨማሪ ይህ አገልግሎት በተሻለ ሊሰጥ ይችላል ተብሎ የታሰበው በባንኩ

ነው። በዚሁ መሠረት ይህን አገልግሎት ለሕብረተሰቡ እንዲሰጥ መንግስት ሥራውን ሰጥቶታል።

ዜልባ፡- ይህ ተልዕኮ ለባንኩ የተሰጠው መቼ ነው? አሁን ያለበት ደረጃስ ምን ይመስላል?

አቶ ተሾመ፡- ባንኩ ኃላፊነት ተሰጥቶት ወደ ሥራ እንዲገባ የተደረገው እ.አ.አ. ከጃንዋሪ 1 ቀን 2016 ጀምሮ ነው። እንቅስቃሴውም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል። በተለይ በዚህ የ2016/17 ዘጠኝ ወር ጊዜ ውስጥ ከሰባት ቢሊዮን ብር በላይ ጥያቄዎችን ተቀብሎ ሥራዎችን በማካሄድ ላይ ይገኛል።

ዜልባ፡- የባንኩ ቅርንጫፎች መብዛት ከሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አለው?

አቶ ተሾመ፡- የቅርንጫፎች ብዛት ከሊዝ ፋይናንሲንግ ሥራ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አለው። ይህ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ የሚሰጠው በቅርንጫፎች ነው። ስለዚህ ከተደራሽነት፣ ውጤታማ ከማድረግ እንዲሁም ከማስፋት አንጻርም አዳዲስ ቅርንጫፎችን መክፈት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። በዚሁ መሠረት በርካታ ሠራተኞች እንዲሁ ተቀጥረዋል፤ እየተቀጠሩም ይገኛሉ። እንደዚሁም ከቅርንጫፎች አካባቢ ከሚሰጠው አገልግሎት 70 በመቶው የሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎት እንዲሰጥ ነው ከመንግሥት በኩል አቅጣጫ የተሰጠው። ባንኩም ይህንን ወስዶ በስትራቴጂክ ዕቅድ እና በዓመታዊ ዕቅዱ ውስጥ አስገብቶ ወደ ሥራ ገብቷል። በዚህም የተነሳ የቅርንጫፎች ብዛት በቀጥታ ከሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት ጋር የተገናኘ ነው ማለት ይቻላል።

ዜልባ፡- የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎቱ በዕቅዱ መሠረት እየተከናወነ ነው?

አቶ ተሾመ፡- በዕቅዱ መሠረት በተለያዩ ምክንያቶች ሙሉ በሙሉ ባይከናወንም ጅምሩ አለ። ለዚህም በምክንያትነት የሚቀመጡ ነገሮች አሉ። በመጀመሪያ ታሳቢ የተደረገው ይህ አገልግሎት መንግሥት ባዘጋጃቸው የማምረቻ ቦታዎች (ክላስተሮች) ላይ ነበር። እነዚህን የማምረቻ ቦታዎች ወደ ሥራ ከማስገባት አንጻር ዉስንነት በመኖሩ በእነዚህ ቦታዎች ወደ አገልግሎት ገብተው ይህ አገልግሎት ያልተሰጠበት ሁኔታ አለ። አገልግሎቱም አሁን እየተሰጠ ያለው በግል የማምረቻ ቦታ ያላቸው ወይም ተከራይተው ለመጡ ኢንተርፕራይዞች ነው። ይህን አገልግሎት በሥፋት እያገኙ ያሉት እነዚህ ኢንተርፕራይዞች ናቸው። እንግዲህ ይህ ችግር ለወደፊቱ እየተፈታ ሲሄድ አገልግሎቱ የሚሰፋበትና

Page 21: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 17

በዕቅዱ መሠረት ሂዶ ግቡን የሚመታበት ሁኔታ ይኖራል ብለን ነው የምንገምተው። ይህንንም ከማሣካት አንጻር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር እየተነጋገርን፣ ችግሮችን እየፈታን እየሄድን ያለንበት ሁኔታ ነው ያለው። የማምረቻ ቦታዎች ውስንነት አለ። ያሉትም ቢሆን በፍጥነት ወደ ሥራ ከመግባት አኳያ ችግሮች አሉ። እንዲሁም ባለድርሻ አካላትም ጉዳዩን ተገንዝበው በፍጥነት ወደ ሥራ መግባት ላይ ክፍተት በመኖሩ በዕቅዱ መሠረት ወደ ፊት ለመሄድ አልተቻለም።

ዜልባ፡- በሥራ ሂደት ያጋጠሙ ችግሮች ምንድናቸው?

አቶ ተሾመ፡- ብዙ ችግሮች ሊኖሩ ይችላሉ። በዋናነት ግን ከላይ ያነሳናቸው ናቸው። በተጨማሪም በውስጥ አቅም ያለው ችግር ደግሞ አገልግሎቱ አዲስ ከመሆኑ አንጻር የተለያዩ መመሪያዎችንና አሠራሮችን መቅረጽ ያስፈልግ ነበር፤ ይህም የተወሰነ ጊዜ ወስዷል። እንዲሁም ያለው የሥራ አመራርም ሆነ ባለሙያ በቶሎ ተነሳሽነቱን ወስዶ ወደ ሥራ ከመግባትም አኳያ ክፍተት እንዳለ መገንዘብ ተችሏል።

ዜልባ፡- እነዚህን ችግሮችስ ለመፍታት የተወሰዱ መፍትሔዎች ምንድናቸው?

አቶ ተሾመ፡- ችግሮችን ለመፍታት አስፈላጊ ናቸው የተባሉ ሥልጠናዎች፣ የማስተዋወቅ ሥራዎች፣ የአሰራር መመሪያዎችን አዘጋጅቶ የማጸደቅ ሥራዎች፣ ወደ ሥራ የመግባት ሁኔታዎች እንዲሁም ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የቀረበ ግንኙነት ፈጥሮ መሄድን በተመለከተ የተለያዩ ሥራዎች ተሰርተዋል፤ እየተሰሩም ይገኛሉ። ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለው የሥራ ግንኙነት ከተለያዩ የክልል ካቢኔ አባላት እንዲሁም ከፌዴራል መ/ቤቶች ጋር ስለ ሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎት ገለጻና ምክክር ተደርጓል። ከዚህ በመነሳት እንዲሁ አንዳንድ ክልሎች የባንኩን የሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎት ያካተተ ስትሪንግ ኮሚቴ አቋቁመው በመሥራት ላይ ይገኛሉ።

ዜልባ፡- የሊዝ ፋይናንስ ሥራን ለማከናወን የተቀመጡ ታሳቢዎች በተግባር ካለው ጋር ምን ያህል ይጣጣማሉ? ተግባራዊነታቸውስ ጊዜን ጨምሮ ምን ይመስላል?

አቶ ተሾመ፡- ቀደም ሲል አንዱ ታሳቢ ያልኩት የተዘጋጁ የማምረቻ ቦታዎች ናቸው። ይህም በፍጥነት ሥራ ላይ አልዋለም። ሌላው በአሠራራችንም እንዲሁ ሁኔታዎችን እያየን የምናሻሽላቸው የአሰራር መመሪያዎች፣ በተለይ በግዥ አካባቢ ያሉ ዳታ ቤዞች እንዲሁም በጨረታ በጥቅል ግዥ ለማካሄድ ዓለምአቀፍ ጨረታ ውስጥ የገባንባቸው መሳሪያዎች እንዲሁ ጊዜ ወስደዋል። እነዚህ ሁኔታዎች ከዕቅዳችን ውጭ እንድንሆን አድርገውናል። ምክንያቱም እኛ ያሰብነው ይህን አገልግሎት እንሰጣለን ያልነው በግለሰብ ደረጃ ነበር። ሆኖም ግን አንዳንድ ግዥዎች ወደ ጥቅል ግዥ እንድንገባ አድርገውናል። አንዳንድ ግዥዎች ደግሞ የውጭ አገር ግዥዎች በመሆናቸው ከሰነድ ዝግጅት ጀምሮ፣ ከሚመለከታቸውን የዕቃ አምራች ወይም አቅራቢ ድርጅቶች ጋር የመረጃ ልውውጥ ተደርጎ፣ ጨረታውን አወዳድሮ መስጠትና በዚያ መሠረት መሳሪያዎችን መረከብ ጊዜ ወስዷል። እንዲሁም የተረከብናቸውን ማመልከቻዎች ቶሎ ፕሮሰስ አድርጎ፣ ብድሩ እንዲፈቀድና እንዲለቀቅ ከማድረግ አኳያም እንዲሁ በተለያዩ ምክንያቶች መጓተት ፈጥረውብናል። ይህንንም ለመቅረፍ ተጨማሪ ሠራተኞችን መቅጠር፣ አንዳንድ አሠራሮቻችንን ማሻሻል እና የመሣሠሉትን ሥራዎች እየሰራን እንገኛለን።

ዜልባ፡- ከካፒታል ዕቃዎች አቅርቦት ጋር በተያያዘ ያሉ አስቻይ ሁኔታዎችና ተግዳሮቶች ምን ይመስላሉ?

አቶ ተሾመ፡- አስቻይ ሁኔታዎች አሉ። ከፍተኛ የሆነ ፍላጎት አለ። ሰዎች ወደ ሥራ ገብተው ለማምረት ጉጉት እንዳላቸውና ከዚህም አኳያ ጥያቄዎቻቸውን እያቀረቡ ያለበት ሁኔታ አለ። ይህን ተከትሎ ባንኩም ለማበደር መዘጋጀቱ እንዲሁ እንደ አስቻይ ሁኔታ ይወሰዳል። ተግዳሮቶቹ ላይ ስንመጣ እንዲሁ የማምረቻ ቦታ ችግር ከዚህ ጋር በተያያዘ የኃይል አቅርቦት፣ የመሠረተ ልማት አገልግሎቶች ክፍተት አለ። እንዲሁም በባለድርሻ አካላት አካባቢ ተቀናጅቶ ለአንድ ዓላማ ከመሰለፍ አንጻር ክፍተት እንዳለ ነው የሚታየው። ጠቅለል ባለ መልኩ ዋና ዋናዎቹ እነዚህ ናቸው።

ዜልባ፡- በሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት የትግበራ ሥራ ውስጥ እንደ ስኬት የሚታዩ ነገሮች ምንድናቸው?

አቶ ተሾመ፡- እንግዲህ ሊዝ ፋይናንሲንግ ለአገሪቱም ሆነ ለባንኩ አዲስ ምርት ነው። በአጭር ጊዜ ውስጥ ባንኩ 75 አዳዲስ ቅርጫፎችን ከፍቶ፣ ሠራተኞችን ቀጥሮና አሰልጥኖ፣ ቢሮና የቢሮ ፋሲሊቲ አሟልቶ፣ መሳሪያ ገዝቶ ወደ ስራ ገብቶ ሊዝ ፋይናንሲንግን ማስተዋወቁና እንዲሁ ከደንበኞች ጥያቄዎችን ተቀብሎ ማስተናገዱ እንደ ትልቅ ስኬት ይታያል።

ዜልባ፡- በተጨማሪ የሚያስተላልፉት መልዕክት ካለ?

አቶ ተሾመ፡- አሁን ለመንግሥት ለማቅረብ አንድ ፕሮፖዛል አዘጋጅተናል። ፕሮፖዛሉ ላይ አንደኛ ነባር የአነስተኛና መካከለኛ ክላስተሮች ወደ ሥራ እንዴት እንደሚገቡና ከባንኩ የሊዝ ፋይናንሲንግ ሥራ ጋር በማገናኘት የባንኩን የሊዝ ፋይናንሲንግ መስፈርቶች የሚያሟሉ ኢንተርፕራይዞች ወደ ሥራ የሚገቡበትን አካሄድ ምን መሆን እንደሚችል አስቀምጠናል። ሁለተኛው እንደ አዲስ የሚቋቋሙ የአነስተኛና መካከለኛ ክላስተሮች ባንኩ በግንባታው ሂደት የራሱን ድርሻ መወጣት እንዳለበት ያሳየንበት ሁኔታ ነው ያለው። አንዱ በሥራ ሂደት እንዳየነው ትልቁ የመሠረተ ልማት፣ የማምረቻ ሼዶች እጥረት በአገሪቱ አለ። ስለዚህ መንግሥት እነዚህን ክላስተሮች በመገንባት ለተጠቃሚዎች በኪራይ በማስተላለፍ ባንኩም ደግሞ ብቃት ያላቸውን ኢንተርፕራይዞች የሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎት መስጠት የሚለው ተቀናጅቶ በዚህ መልክ የሚሠራ ነው። ይህም በዘርፉ የተቀመጠው ዓላማ ግቡን እንዲመታ ያስችላል። ስለዚህ ባንኩ መሠረተ ልማቶች እና ፋሲሊቲዎችን በአንድ ቦታ ላይ በጋራ እንዲጠቀሙ የሚያስችሉ ክላስተሮችን ከማቋቋም አንጻር የበኩሉን አስተዋጽኦ ማበርከት ስላለበት ለከተማ አስተዳደሮች ብድር በመሥጠት ይህን ፋሲሊቲ እንዲያዘጋጁና በባንኩ መስፈርቶች ደግሞ ተጠቅሞ ከቢዝነስ ኮሚዩኒቲ የተመለመሉ ባለሃብቶች ወይም ኢንተርፕራይዞች በኪራይ መልክ ወደዚህ አገልግሎት እንዲገቡና ከባንኩ ደግሞ በሊዝ ፋይናንሲንግ ማሽነሪ የሚያቀርብበት አሠራር እንዲኖር ነው ፕሮፖዛሉን ያዘጋጀነው።

በአጠቃላይ ይህ የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት በአገሪቱ ትልቅ ለውጥ ሊያመጣ የሚያስችል ሥራ ነው። ምክንያቱም የሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎት አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በአገሪቱ ውስጥ በስፋት እንዲኖሩ የሚያደርግ፤ ከእርሻ ወደ ኢንዱስትሪ የሚደረገውን የትራንስፎርሜሽን ሽግግር የሚያሳልጥ እና የስራ ዕድልም በሰፊው የሚከፍት ነው። ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን የሚተኩ (Import Substitution) እንዳስፈላጊነቱም ወደ ውጭ ለመላክ (Export) አስፈላጊ የሆኑ ምርቶችን የሚያመርቱ ካምፓኒዎች ናቸው ማለት ይቻላልና ከሥራው ስፋት አንጻር ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው እና ዓላማውንም እንዲሁ ተገንዝበው ለስኬት ጠንክረው መሥራት እንደሚኖርባቸው በዚሁ አጋጣሚ ለመግለጽ እወዳለሁ፤አመሰግናለሁ።

Page 22: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et

ከስራ ክፍሎቻችን

18

ዜ.ል.ባ፡- የውጭ ንግድ ብድር ዋስትናና የልዩ ብድር አስተዳደር ዳይሬክቶሬት (ECG) በባንኩ ውስጥ ያለው ጉልህ ድርሻ ምንድነው?

ወ/ሮ የመንዝወርቅ፡- የወጭ ንግድ ብድር ዋስትና መንግስት የአገር ውስጥ ላኪዎችን ለማበረታታትና በዚያውም የውጭ ምንዛሬ ገቢን ለማሳደግ የተዘጋጀው ማበረታቻ ሲሆን አሰራሩም አበዳሪ ባንኮች (ንግድ ባንኮች)፣ ላኪዎች (ከቡና ላኪዎች በስተቀር) ለሚሰጠው ብድር 80% በዋስትና በመሸፈን የብድር አቅርቦትን ማዘጋጀት ነው፡፡ ይህ ሥራ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በኩል ሲሰራ ቆይቶ እ.ኤ.አ ከየካቲት 1 ቀን 2007 በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በተፃፈ ደብዳቤ ወደ ባንካችን ተላልፏል፡፡

በዚህም መሠረት ባንካችን ሥራውን ለመተግበር የሚያስፈልገውን ቅድመ ሁኔታ ለማዘጋጀት በወቅቱ የቅርንጫፍ ማስተባበሪያ መምሪያ በሚባለው የሥራ ክፍል ውስጥ ሁለት የብድር መኮንኖችን በመመደብ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ተይዘው የነበሩ የብድር ዋስትና ሰነዶችን በመረከብ ሥራውን ጀምሯል፡፡

በመቀጠልም ሥራው ትኩረት የሚገባው መሆኑንና የብድሩን መጠን ከግንዛቤ በማስገባት አንድ የሥራ ክፍል ኃላፊና በሥሩ ሌሎች አራት የብድር መኮንኖችን አካትቶ የልዩ ብድር አስተዳደር ሥራን በመጨመር የፕሮጀክት አስተዳደር ዋና ክፍል በሚል መጠሪያ በቀድሞ መጠሪያው የቅርንጫፍ ማስተባበሪያ መምሪያ ውስጥ ተካቶ እንዲሠራ ተወሰነ፡፡

ባንኩ ለሁለተኛ ጊዜ ባደረገው የBPR እና Structural ለውጥ እ.ኤ.አ በ2008 የክፍሉን ኃላፊነትና የሥራ ፍሰት ከግምት ውስጥ በማስገባት ክፍሉ ራሱን ችሎ በመምሪያ ደረጃ የውጭ ንግድ ብድር ዋስትናና የልዩ ብድር አስተዳደር ቢሮ በመባል ተዋቅሮ በቀድሞ መጠሪያው Client Relation and Branch Operation ምክትል ፕሬዝዳንት ሥር ተደራጀ፡፡

የሥራ ክፍሉ በአሁኑ ጊዜ “የውጭ ንግድ ብድር ዋስትናና የልዩ ብድር አስተዳደር ዳይሬክቶሬት” የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን በም/ፕ ክሬዲት ማኔጅመንት ሥር ተዋቅሮ ሥራውን እያከናወነ ያለ ዳይሬክቶሬት ነው፡፡

የውጭ ንግድ ብድር ዋስትና ወደ ባንኩ በሚመጣበት ወቅት በብር 400 ሚሊዮን የማይበልጥ የብድር ክምችትና 50 ሚሊዮን የሚሆን የዋስትና መጠባበቂያ ገንዘብ ይዞ ሥራውን የጀመረ ሲሆን በሂደት ወደ ባንካችን ከመጣ በኋላ የዋስትና ብድር መጠኑ በአንድ ወቅት በዓመት እስከ ብር 1.6 ቢሊዮን የደረሰ መሆኑ ይታወሳል፡፡ በመቀጠልም ከጊዜ ብዛት ይህ የዋስትና የብድር ክምችት እየቀነሰ የመጣ ሲሆን በተመሳሳይ መንገድም የዋስትና አገልግሎቱን የሚጠቀሙ የአበዳሪ ባንኮች ብዛትም እየቀነሰ የመጣ መሆኑ ይታያል፡፡

ይህ ሊሆን የቻለበት አንድም ላኪዎቹ ባገኙት የዋስትና ብድር ገቢ የራሳቸው የሆነ በቂ ካፒታል በማግኘታቸው ይህንን እንደዋስትና በማቅረብ ከባንኮች ብድር ማግኘት ያላስፈለጋቸው በመሆኑ፣ ሌላም አበዳሪ ባንኮች ከላኪዎቹ ጋር በፈጠሩት የሥራ ግንኙነት መሠረት በላኪዎቹ ላይ በፈጠሩት እምነት ብድሩን በአነስተኛ ዋስትናና በቀጥታ ያለዋስትና እየሰጡ በመሆኑ ነው ተብሎ ይገመታል፡፡

ዳይሬክቶሬቱ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ የተለያዩ የሥራ ሂደቶች ውስጥ በመሳተፍ ለባንኩ ጉልህ የሆነ ድርሻ እያበረከተ ነው፡፡ ይህም በሚከተሉት ሁኔታዎች ሊገለጽ ይችላል፡፡

በውጭ ንግድ ብድር ዋስትና ረገድ፡-

ሥራው ወደ ባንኩ ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ በ12 ባንኮች በኩል እስከ ብር 4.2 ቢልዮን ለ276 የውጭ ምርት ላኪዎች የብድር ዋስትና ሽፋን የሰጠ መሆኑ የታወቃል፡፡

በዚህም መሠረት የቅባት እህሎች፣ ጥራጥሬ፣ የቆዳ ውጤቶች፣ የጨርቃጨርቅና ቅመማቅመም እንዲሁም ሰምና የሰም ምርቶችን ጨምሮ ልዩ ልዩ ወደ ውጭ የሚላኩ የግብርና ምርቶች የዋስትና ድጋፍ ተጠቃሚ የሆኑ የሥራ መስኮች ናቸው፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ለመጠባበቂያ ከተቀመጠው 50 ሚሊዮን ብር ባንኩ በተለያየ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውና ብድራቸውን በአግባቡ ለአበዳሪ ባንኩ መክፈል ላቃታቸው ተበዳሪዎች ብር 19.6 ሚልዮን ለዋስትና በገባው ግዴታ መሠረት ተከፋይ አድርጓል፡፡

እንዲሁም ይህንን አገልግሎት በመስጠት ከአበዳሪ ባንኮች ከተገኘው የዋስትና ክፍያ ብር 48.1 ሚልዮን ተገኝቷል፡፡ ይህ ለመጠባበቂያ ከተያዘው ጋር ተጨምሮ ብር 98.1 ሚልዮን የደረሰ ሲሆን በወቅቱ ለሚመለከተው የመንግሥት አካል ፈሰስ ተደርጓል፡፡

በአጠቃላይ ይህ ሥራ በመሰራቱ አገሪቱ በአማካይ የUSD 565.5 ሚልዮን የውጭ ምንዛሪ ገቢ ያገኘችና ባንኩም ለዚህ ገቢ ዋነኛ አስተዋጽኦ አድራጊ መሆኑ ይታወቃል፡፡

በገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን ረገድ፡-

ባንኩ ከውኃ መስኖና ኤሌክትሪክ መ/ቤት ጋር ባደረገው የአደራ ገንዘብ ማስተዳደር ውል መሠረት ከPhase 1 እስከ Phase 4 ድረስ የገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮጀክቶች የማስተዳደር ውል ፈርሟል፡፡ የገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮጀክቶችን ባንኩ ሲያስተዳድር የአገልግሎት ክፍያ ይቀበላል፡፡ በመሆኑም ዳይሬክቶሬቱ ለባንኩ ተጨማሪ ገቢ የሚያስገኝ ሥራ እያከናወነ ያለ መሆኑ ግንዛቤ ሊወሰድ ይገባል፡፡

ይህ የገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን ሥራ ለባንኩ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ከመሆኑ ባሻገር እስካሁን ለ654 በኮኦፕሬቲቭ ለተደራጁ ማህበራት በጸሐይ ኃይል የሚሠሩ ብርሃን እና ሌሎች አገልግሎት የሚሰጡ ቴክኖሎጂዎችን ያሰራጨ ሲሆን የገጠሩን ህብረተሰብ የኃይል አቅርቦት ፍላጎት በማሟላት

ከቀድሞዋ የንግድ ብድር ዋስትናና የልዩ ብድር አስተዳደር ዳይሬክተር (ECG) ወ/ሮ የመንዝወርቅ ግረፌ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ

Page 23: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 19

የልማት አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ ከዚህም ፕሮጀክት ከ40 ሺ በላይ የሚደርሱ አባወራዎች የተጠቀሙ ሲሆን በእያንዳንዱ ቤተሰብ በአማካይ 5 የቤተሰብ አባል ቢገኝ ከ200 ሺ በላይ የሆነ የህብረተሰብ ክፍል የብርሃን አገልግሎት ማግኘቱ ባንኩንም ሆነ በዳይሬክቶሬቱ ውስጥ እዚህ ፕሮጀክት ላይ አስተዋጽኦ ያላቸውን ሠራተኞች የሚያኮራ ተግባር ነው፡፡ ከዚህም ባሻገር የዚህ በፀሐይ ኃይል የሚሠሩ መሳሪያዎች መተከል የሚተኩትን የኩራዝ ብዛትና ወደ አየር የሚለቀቅ የካርቦንዳይኦክሳይድ መጠን በመገንዘብ በካርቦን ልቀት ዙሪያ ለአገሪቱ የሚሰጠው ጠቀሜታ የባንኩ አስተዋጽኦ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡

በታዳሽ ኃይልና ኃይል ቆጣቢ የገበያ አቅርቦት ብድር ረገድ፡-

የኢትዮጵያ መንግስት የታዳሽ ኃይልና ኃይል ቆጣቢ ገበያ ለማጎልበት ባለው ዕቅድ ከዓለም ባንክ ጋር ባደረገው ስምምነት በግል አልሚዎችና በአነስተኛና ጥቃቅን ብድር አቅራቢ ድርጅቶች በኩል የሚሰራጭ ብድር ባመቻቸው መሠረት ባንካችን ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ትብብር ሚኒስቴር ጋር ባደረገው የብድር ስምምነት ለግል አልሚዎች የሥራ ማስኬጃ የሚሆን ገንዘብ በማመቻቸት እየሠራ ይገኛል፡፡

በዚህም ረገድ ፕሮግራሙ ከተጀመረ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ለ8 የግል አልሚዎችና ለ5 ማይክሮፋይናንሶች ብድር በመስጠት ከ800,000 በላይ አነስተኛ መብራቶችን (So-lar Lantern) በግል አልሚዎችና በማይክሮፋይናንሶች በኩል፣510 Solar Home Systems፤ 1012 Biogas፤40 ICS ፤245; 424 CFL እና 36,000 Led Lamps ሊያሠራጭ የቻለ ሲሆን በዓለም ባንክ ግምገማ መሠረት የተሰራውን ሥራ አመርቂነትና በሂደት ላይ ያሉ ጥያቄዎችን ከግምት በማስገባት ተጨማሪ ብድር የተፈቀደ በመሆኑ በቀጣይ ዓመታት ከዚህ የተሻለ በፀሐይ ኃይል የሚሰሩና ታዳሽ ኃይልና ኃይል ቆጣቢ ምርቶችን ለገጠሩ ህብረተሰብ ተደራሽ እንደምናደርግ ለመግለጽ እወዳለሁ፡፡

እነዚህ ምርቶች በገጠሩ ህብረተሰብ አካባቢ ለሚቀንሱት የካርቦን ልቀት መተኪያ አግባብ ያለው ገቢ አገሪቱ የምታገኝ መሆኑን በዚህ አጋጣሚ ለመግለጽ እየወደደኩ ለዚህ ገቢ የሚያመቻቹ፣

1. Ethiopian Clean Cooking

2. Ethiopian Off-grid Renewable Energy የተባሉ ፕሮግራሞችን ባንኩ በUNFCCC አስመዝግቦ ቅድመ ሁኔታዎችን እንዲሁም የካርቦን ልቀት ቅናሽ ሽያጭ ውል ያደረገ በመሆኑ ባንኩ የሚጠበቅበትን የልማት ድርሻ በአግባቡ እያከናወነ ስለመሆኑ ስገልጽ በደስታ ነው፡፡

በተጨማሪም ክፍሉ አነስተኛ የግል አልሚዎች በብዛት የብድሩ ተጠቃሚ እንዳይሆኑ ሲያግዳቸው የነበረውን የዋስትና ችግር ለመፍታት ከዓለም ባንክና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው መንግስታዊ ተቋማት ጋር ውይይት በማድረግ ለሚበደሩት ብድር 50% ተጨማሪ የብድር ዋስትና ገንዘብ በማመቻቸት የግል አልሚዎች እንዲበረታቱና ወደ ኃይል ቆጣቢና በፀሐይ ኃይል የሚሰሩ ዕቃዎች አቅርቦት ሥራ እንዲገቡና ህብረተሰቡን ጠቅመው እራሳቸውንም እንዲጠቅሙ እየሠራ መሆኑን በዚህ አጋጣሚ ለማብሰር እወዳለሁ፡፡

ከዚህም ሌላ ባንኩ ከUNDP ጋር ባደረገው ግንኙነት ለኃይል ቆጣቢና በፀሐይ ኃይል የሚሰሩ ቴክኖሎጂዎች ለመጠቀምም ሆነ ለማምረት ከግል ባንኮች ለሚወሰዱ ብድሮች የብድር ዋስትና ለመስጠት አሠራሮችንና የተጠቃሚዎችን መስፈርት በማዘጋጀት በቅርብ ቀን ወደ ሥራ ለመግባት ዕቅድ የተያዘ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የሴት ሥራ ፈጠራ ክህሎት ልማት ፕሮግራም (WEDP) ረገድ፡-

WEDP በክፍሉ ውስጥ ከሚተዳደሩ የልዩ ልዩ ብድር አገልግሎት ውስጥ አንዱ ነው። ይህ ፕሮግራም ባንኩ እንደ ዋና ተግባሪ አካል ከተመረጠበት ከ2012 ዓ.ም. ጀምሮ የአገሪቱ ግማሽ የሰው ብዛት ያካተተውን የሴቶችን የሥራ ፈጣሪነትና ክህሎት ለማሳደግ እየተንቀሳቀሰ ያለ ፕሮግራም ነው፡፡ ፕሮግራሙ ሲቀረጽ በ6 ዋና ዋና ከተሞች ውስጥ ሐዋሳን፣ ባህርዳርን፣ መቀሌን፣ አዳማን፣ አዲስ አበባን እና ድሬዳዋን ይዞ ከተሞቹ በ50 ኪሎ ሜትር ርቀት ዙሪያ የሚያካልሉትን አነስተኛ ከተሞች በመጨመር የሴት ሥራ ፈጣሪዎችን ለመደገፍ ተዘጋጅቷል፡፡

በዚህም ረገድ ባንኩ ቀደም ሲል ከ8 የአነስተኛ ብድር አቅራቢ ተቋማት ጋር በመስራት ብድሩን ከላይ በተጠቀሱት በኩል ለማዳረስ ችሏል፡፡ በመቀጠልም 4 ተጨማሪ የአነስተኛ ብድር አቅራቢ ተቋሞችን በመጨመር ተደራሽነቱን ለማስፋት ተንቀሳቅሷል፡፡

በመሆኑም WEDP የብድር መጠኑን ከፍ በማድረግና የአነስተኛ ብድር አቅራቢ ተቋማት የተመቻቹበትን የቡድን ዋስትና ብድር ወደ ግል ብድር በማለማመድና በቂ ስልጠና በመስጠት የተጀመረ ፕሮግራም ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ብድሩ ሊሰራጭ ከታሰበበት የ5 ዓመታት ፕሮግራም በአጠረ ጊዜ ውስጥ ባንኩ ብድሩን በ3 ዓመታት አሰራጭቶ አጠናቋል፡፡

የፕሮራሙ የግማሽ ክፍለ ጊዜ ግምገማ እንዳሳወቀው ፕሮግራሙ ከተቀመጠለት ግብ አኳያ አመርቂ ውጤት ያስመዘገበ መሆኑን ገምግሟል፡፡

ይህንን ውጤት መሠረት በማድረግና የታየውን የሥራ ፈጣሪዎች ተጨማሪ የገንዘብ ፍላጎት በመመልከት የተለያዩ የብድር አቅራቢ አካላት ተጨማሪ ብድር ለመስጠት ከመንግሥት ጋር ድርድር በማድረግ ላይ በመሆናቸው እ.ኤ.አ በ2017 የሴት የሥራ ፈጣሪዎችን ለመደገፍ በቂ የብድር ገንዘብ ይገኛል ተብሎ ይታሰባል፡፡

የ WEDP ፕሮግራምን ከሌሎች ፕሮግራሞች ለየት የሚያደርገው ሴት የሥራ ፈጣሪዎች የብድር ገንዘብ አቅርቦት ድጋፍ ብቻ ሳይሆን ክህሎት ማዳበሪያ ስልጠናም አብሮ በቅንጅት የተዘጋጀ መሆኑ ነው፡፡

እ.ኤ.አ እስከ መስከረም 30 2009 ድረስ ከዓለም ባንክ በተገኘው የብድር ገንዘብ ለ4,421 የሴት ሥራ ፈጣሪ ተበዳሪ ድርጅቶች የብድር ድጋፍ የተደረገ ሲሆን እነዚህ ድርጅቶች በአማካይ እስከ 5 ሠራተኞች በየድርጅቱ ቢቀጥሩ ከ22 ሺ በላይ ለሆኑ ሥራ አጦች የሥራ እድል ተፈጥሯል ለማለት ይቻላል፡፡ ይህ በእንዲህ እያለ ከዓለም ባንክ ከተገኘው ብድር በተጨማሪ ከአነስተኛ የብድር አቅራቢ ተቋማትና ከባንካችን በተገኘ የመልሶ ማበደር ተግባር የተበዳሪዎች ቁጥር ወደ 5,337 ከፍ ሊል የቻለ መሆኑን ከየተቋማቱ የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡ ይህንንም እያንዳንዱ ድርጅት በአማካይ በሚፈጠረው የሥራ እድል ስናባዛው ከ27 ሺ በላይ ወይም ተጨማሪ 5 ሺ በላይ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ተችሏል ማለት ነው፡፡

በአጠቃላይ ይህ ፕሮግራም ለሚቀጥሉት 5 ዓመታት በዚህ ሥራ ላይ የሚቆይ በመሆኑ ምን ያህል የሥራ እድል እንደሚፈጥርና ምን ያህል የሴት የሥራ ፈጣሪዎችን የራሳቸው ድርጅት ባለቤት እንዲሁም የገቢ ምንጭ ሊሆን እንደሚችል መገመት ይቻላል፡፡

በአነስተኛና መካከለኛ ፕሮጀክቶች የብድር ድጋፍ ረገድ፡-

በቅርቡ መንግሥት በአነስተኛና መካከለኛ ፕሮጀክቶች ላይ ለተሰማሩ አልሚዎች ባሰበው የሊዝ ብድር አቅርቦት ድጋፍ ከዓለም ባንክ የተገኘ ብድር አቅርቦት በባንኩ በኩል በሁለት መስኮቶች ብድሩን ለተጠቃሚዎች ለማዳረስ ዝግጅቱ ተጠናቆ ወደ ትግበራ ለመግባት በዝግጅት ላይ ነው፡፡

Page 24: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et

ከስራ ክፍሎቻችን

20

ይህ ብድር በመስኮት 1 በቀጥታ በባንኩ ዋና መስሪያ ቤትና በቅርንጫፎች በኩል ለአነስተኛና መካከለኛ አምራቾች፣ አግሮ ፕሮሰሲንግ፣ እርሻና እንዲሁም ግንባታ (Construc-tion) እና ቱሪዝም ዘርፍ ለሚሰማሩ ተበዳሪዎች የሚሰጥ ብድር ነው፡፡ በዚሁ መስኮት ስር የሚስተናገዱት ቢሆኑም እነዚህም አስከ ብር አንድ ሚሊዮን የሚሆን የካፒታል ዕቃዎች ለመግዛት ለሚፈልጉ አልሚዎች ብድር የሚያቀርብ ነው፡፡

በሁለተኛ ብድር መስኮት ደግሞ ለሥራ ማስኬጃ ብድር ከዚህ በላይ በተጠቀሱት ሥራዎች ላይ ለሚሰማሩ አልሚዎች በንግድ ባንኮች፣ በአነስተኛ የብድር አቅራቢ ተቋማትና የካፒታል እቃዎች አቅራቢ ድርጅቶች በኩል የሚስተናገድ የጥቅል ብድር ወይም (Whole Sale) ብድር ተጠቃሚዎች ይሆናሉ፡፡ ስለዚህ ይህ ዳይሬክቶሬት በጥቅል ብድር ወይም በWhole Sale ለሚሰጡ ብድሮች አቅርቦት ጥናት በማዘጋጀት ክትትል የማድረግና ከዓለም ባንክ ብድሮችን ማስለቀቅ፣ ለየመስኮቶቹ ብድሮችን ማከፋፈልና ሪፖርቶችን የማዘጋጀት ኃላፊነት ተጥሎበታል፡፡ ለዚህም ሥራ የProject Management Team በዳይሬክቶሬቱ ውስጥ ቀደም ሲል ለWEDP ሥራ ከተመደበው የሰው ኃይል ተጨማሪ ተደርጎ ይከናወናል፡፡

በአሁኑ ጊዜ ዳይሬክቶሬቱ ከውጭ በመጡና በEP (En-terprise Partners) ስር ባሉ አማካሪዎች በመታገዝ የ16 የአነስተኛ የብድር አቅራቢዎችንና 12 የንግድ ባንኮችን የቅድመ ብድር ብቃት ምርመራና የDue-Diligence ሥራዎችን አጠናቋል፡፡

በመቀጠልም የብድር ጥናትና ትንተና ሥራውን በቅርብ ቀን አጠናቆ የብድሩን ገንዘብ ብቁ ለሆኑት ተቋማት ለማሰራጨት እየሠራ ነው፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ዳይሬክቶሬቱ ከቻይና ልማት ባንክ ለተገኘው ብድር ባንኩንና የቻይና ልማት ባንክን ከብድሩ ጋር በተገናኘ በማስተባበርና ልዩ ልዩ የጥናት ድጋፎችን፣ መረጃዎችን እና በተያያዥ የሚነሱ ጥያቄዎቸ በማስተናገድ የሁለት ዙር የብድር አቅርቦት ላይ ድጋፍ አድርጓል፡፡ ለሦስተኛ ጊዜ ለሚደረገው ድርድርም ድጋፉን እየሰጠ ይገኛል፡፡ ከዚህ በላይ በተነሱት ሥራዎች ዙሪያ ብድር አቅራቢ የውጭ አካላት በባንኩ ላይ እንዲተማመኑና የተሰራውን ሥራ አመርቂነት በመገንዘብ በየመድረኩ የባንኩን ትልቅነት እንዲመሰክሩ እንዲሁም በተለያዩ የውጭ መድረክ ላይ በተለይም በኢነርጂ መስክ ባንኩ ያደረገው አስተዋጽኦ የመማማሪያ ርዕስ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ የዳይሬክቶሬቱ የስራ ባልደረቦችም በዚህ መድረክ ልምዳቸውን አካፍለዋል፡፡

ዜ.ል.ባ፡- ዳይሬክቶሬቱ በብድር አሰጣጥ (Loan Approval) ፣ አለቃቀቅ (Disbursement) እና አመላለስ (Collection) ረገድ ያለው አጠቃላይ አፈጻጸም ምን ይመስላል?

ወ/ሮ የመንዝወርቅ፡- ይህንን ባጭሩ በሰንጠረዥ በማስቀመጥ መመልከት ይቻላል፡፡ (ገፅ 21 ላይ የተቀመጡትን ሰንጠረዦች ይመልከቱ)

ዜ.ል.ባ.፡- በአጠቃላይ በዳይሬክቶሬቱ ሥራ ሂደት የነበሩ መልካም አጋጣሚዎችና ተግዳሮቶች ቢገልጹልን

ወ/ሮ የመንዝወርቅ፡- እንደ መልካም አጋጣሚ የምንወስዳቸው፡-

1. ባንኩ በECG በኩል ለአገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ለማስገባት የውጭ ንግድ ብድር ዋስትና በመስጠት ላኪዎችን አበረታቷል፣

2. በገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን ዙሪያ ከውኃ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር ጋር በጣምራ በመስራት ከኤሌክትሪክ መስመር ውጭ ያለውን የህብረተሰብ ክፍል ከጨለማ ለማውጣት ከፍተኛ ድጋፍ አድርጓል፣

3. ለሴት የስራ ፈጣሪዎች በአነስተኛ የብድር አቅርቦት ተቋማት በኩል የሚያደርገው ድጋፍ የህብረተሰቡ ግማሽ ክፍል የሆኑትን አነስተኛ የሥራ ፈጣሪ ሴቶችን በመደገፍ የራሳቸው የገቢ ምንጭ በማስገኘት የሥራ ፈጠራ ክህሎታቸውን በማሳደግ የራሳቸው የሥራ መስክ ለመፍጠር በማስቻሉ ከፍተኛ የልማት አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ ይህ ፕሮግራም የገንዘብ ድጋፍ ብቻ ሳይሆን የሥራ ፈጠራ ክንውኑን በሥልጠና በማስደገፍ የሴት እህቶቻችንን ችግር በጥቂቱ የሚቀርፍ በመሆኑ እንደመልካም አጋጣሚ ከሚጠቀሱት ውስጥ ዋነኛ ነው ለማለት እችላለሁ፡፡

4. በገበያ ልማትና ታዳሽ ኃይልና ኃይል ቆጣቢ ምርቶች በኩል በአገራችን ያሉ ከኤሌክትሪክ መስመር ውጭ ለሚኖሩት የህብረተሰብ ክፍሎች ብርሃን የሚያገኙበትን ሁኔታ በማመቻቸት የአኗኗር ዘይቤን በመቀየር፣ ከጋዝና ከእንጨት በመሳሰሉት የሚወጣው ጭስ በጤና ላይ የሚያመጣውን ችግር ከማስወገድ አኳያ ያደረገው ድጋፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው ነው፣

5. በአጠቃላይ ክፍሉ ከውጭ የሚመጡ ገንዘቦችን በአግባቡ ለታቀደለት ዓላማ በማዋልና የአገሪቱን ልማት ከመደገፍ አኳያ ከፍተኛ የሆነ አገልግሎት በመስጠቱ ለብድር የዋለው ገንዘብ አቅራቢ የሆኑት የዓለም ባንክና ሌሎች ተመሳሳይ ድርጅቶች ባንኩን በከፍተኛ የአፈፃፀም ብቃት በየስብሰባው ላይ አወድሰዋል፤ በጽሑፍም ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡

6. ከተለያዩ ፕሮግራሞችና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር መስራት በአገልግሎቱ የተሰማሩትን የክፍሉን ሠራተኞች በክህሎት ከፍተኛ ደረጃ ላይ እንዲደርሱና እውቀታቸውም ከፍ እንዲል አስችሏል፡፡

እነዚህን እንደመልካም አጋጣሚ ከገለጽኩኝ በኋላ ሥራዎች ሲሠሩ ሁል ጊዜ አንዳንድ ችግሮች እንደሚያጋጥሙ ሁሉ አንዳንድ ተግዳሮቶች ያጋጠሙ መሆኑን በዚህ አጋጣሚ ለመጠቆም እወዳለሁ፡፡ እነዚህም፡-

1) ፕሮግራሞች ወደ ባንኩ ሲመጡ ከልዩ ልዩ የባለድርሻ አካላት ጋር በጣምራ የሚሰሩ ሥራዎች አብረው ይታቀዳሉ፡፡ ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ ሁሉም ባለድርሻ አካል እኩል ለሥራው አስተዋጽኦ ሳያደርግ ሲቀር ሥራዎች ሲደናቀፉ ይታያሉ፡፡ በመሆኑም የባለ ድርሻ አካላት በትብብርና በጋራ አለመንቀሳቀስ ፕሮግራሞችን ሊያደናቅፍ የሚችል መሆኑ እንደ ችግር ታይቷል፡፡

2) በገበያ ልማትና ታዳሽ ኃይልና ኃይል ቆጣቢ ምርቶች ከወጭ በፀሐይ ኃይል የሚሠሩ ዕቃዎችን የሚያስመጡ ተበዳሪዎች በብዛት ከብድሩ ተጠቃሚ ያልሆኑት ዋስትና ለማቅረብ ባለመቻላቸው በመሆኑ ይህም እንደ አንድ ተግዳሮት ይቆጠራል፡፡

3) በፀሐይ ኃይል የሚሰሩ ዕቃዎች ከውጭ በሚገቡበት ጊዜ ያለው የአሰራርና የእቃዎች ጥራት ቁጥጥር ላይ በሚፈጥረው የጊዜ መጓተት እቃዎች በወቅቱ ተሰራጭተው የብድሩን ገንዘብም በወቅቱ ለመክፈል አለመቻላቸውም እንደ አንድ ችግር ሊጠቀስ የሚገባው ነው፡፡

ዜ.ል.ባ.፡- እነዚህ ችግሮች በምን መልኩ ተፈቱ?

ወ/ሮ የመንዝወርቅ፡- እነዚህን ችግሮች ለመፍታት የባንኩ የማኔጅመንት አባላት ክፍሉ ለሚያቀርባቸው አማራጭ

Page 25: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 21

ለMFI’s የተፈቀደ ብድር

መጠን(ብር)

ለMFI’s የተለቀቀ ብድር መጠን(ብር)

ከMFI’s የተሰበሰበ የብድር መጠን(ብር)

ለMFI’s ያልተለቀቀ የብድር መጠን(ብር)

ለWEDP ተበዳሪዎች የተለቀቀ(ብር)

WEDP ተበዳሪ ፕሮጀክቶች ቁጥር

ለWEDP ተበዳሪዎች ያልተለቀቀ ገንዘብ(ብር)

1,065,723,104

944,196,886 463,130,465 121,526,218 925,563,271 5,337 18,633,615

የችግር መፍቻ የመፍትሔ ኃሳቦች ላይ አስተያየትና ከፍጻሜ እንዲደርስ በማገዝ ችግሮቹ ሙሉ በሙሉ ባይፈቱም አሁን የተገኘው የአፈጻጸም ደረጃ ለመድረስ ተችሏል፡፡

ዜ.ል.ባ፡- ለወደፊቱ በባንኩም ሆነ በሀገር ደረጃ ካለው ሚና በመነሳት በክፍሉ የታቀደ ነገር ካለ?

ወ/ሮ የመንዝወርቅ፡- ECGን በተመለከተ አሁን እየሠራን ያለነው ከጥቂት አበዳሪ ባንኮችና የውጭ ንግድ ላኪዎች ጋር ነው፡፡ ነገር ግን አዳዲስ ላኪዎች ካሉና ከባንክ ብድር ለመውሰድ ዋስትና ባለማቅረባቸው የውጭ ገበያ እድል የሚያመልጣቸው ከሆነ ቀደም ሲል አብረዋቸው ከሚሰሩ ባንኮች የዋስትና ጥያቄ ቢመጣ የምንቀበል መሆኑን አገልግሎቱ አሁንም መኖሩን በዚህ አጋጣሚ ለመጠቆም እወዳለሁ፡፡

የሴት የሥራ ፈጣሪዎች ልማትን በተመለከተ በቅርቡ ከሁለት ዓለምአቀፍ (International) አበዳሪዎች የብድር አቅርቦት በአገሪቱ መንግስት በኩል በድርድር ላይ በመሆኑ በዚህም ዙሪያ ብዙ ተጠቃሚዎችንና ሴት የሥራ ፈጣሪዎችን ተደራሽ ለማድረግ ዕቅድ ያለ መሆኑን ለመግለጽ እወዳለሁ፡፡

እንዲሁም ለገበያ ልማትና ለታዳሽ ኃይልና ኃይል ቆጣቢ ምርቶችን በተመለከተ ባንኩ ተጨማሪ የብድር አቅርቦት ያገኘ በመሆኑ ተጨማሪ አነስተኛ የብድር አቅራቢ

ተቋማትንና የግል ዘርፍ የታዳሽ ኃይልና ኃይል ቆጣቢ ምርት አቅራቢዎችን ለማገልግል ዝግጅታችንን የጨረስን መሆኑን ለማብሰር እወዳለሁ፡፡ ከውጭ ለሚመጡ በጸሐይ ኃይል ለሚሰሩ ዕቃዎች አስመጭ ድርጅቶች የሚገጥማቸውን የዋስትና ችግር ለመፍታት እንዲሁ ባንኩ ከገንዘብ አቅራቢው የዓለም ባንክ ጋር በመነጋገር አነስተኛ የሆነ የዋስትና ፈንድ ያገኘ በመሆኑ የዚህን ዋስትና ለመጠቀም የሚያበቁ መስፈርቶችን የሚያሟሉ አስመጭዎች እስከ 50% የብድሩን ዋስትና ለማግኘት የሚችሉ መሆኑን ለመግለጽ እፈልጋለሁ፡፡

እንግዲህ እነዚህና ሌሎች በጅምርና በድርድር ላይ ያሉ ሌሎች የኢነርጂውን ዘርፍ ትናንሽና መካከለኛ ፕሮጀክቶችን ሊደግፉ የሚችሉ ዕቅዶች መኖራቸውን አሳውቃለሁ፡፡

ባንኩ ከስሙ ለመረዳት እንደሚቻለው የልማት አጋዥና የአገሪቱ የልማት ክንድ በመሆኑ ዋነኛ ተግባሩ ከሆነው ትላልቅና መካከለኛ ፕሮጀቶችን የመደገፍና የረጅምና የመካከለኛ ጊዜ ብድር ከመስጠት ባሻገር የአገሪቱን ልማት ያሳልጣሉ በተባሉና ለህበረተሰብ ድጋፍ ይሰጣሉ ብሎም አገሪቱን ከድህነት ያላቅቃሉ ለተባሉ ፕሮግራሞች ሁሉ ያላሰለሰ ጥረት የሚያደርግ ባንክ ነው፡፡

ለMFI’s የተፈቀደ ብድር መጠን (ብር)

ለMFI’s የተለቀቀ ብድር መጠን (ብር)

ከMFI’s የተሰበሰበ የብድር መጠን (ብር)

ለMFI’s ያልተለቀቀ የብድር መጠን(ብር)

ለMDRE&EEP ተበዳሪዎች የተለቀቀ (ብር)

MDRE&EEP ተበዳሪ ፕሮጀክቶች ቁጥር

ለMDRE&EEP ተበዳሪዎች ያልተለቀቀ ገንዘብ (ብር)

524,251,899.00 348,275,408 200,052,844 100,031,000 65,492,213 30,195 40,109,430

ለግል አልሚዎች የተፈቀደ ብድር መጠን(ብር)

ለግል ልሚዎች የተለቀቀ ብድር መጠን(ብር)

ከግል አልሚዎች የተሰበሰበ የብድር መጠን(ብር)

ለግል አልሚዎች ያልተለቀቀ የብድር መጠን(ብር)

የተበዳሪ ፕሮጀክቶች ቁጥር

256,018,399.00 190,072,907.49 129,553.579.42 52,257,797 8

ለREF የተፈቀደ ብድር

መጠን(ብር)

ለREF የተለቀቀ ብድር መጠን(ብር)

ከREF የተሰበሰበ የብድር መጠን(ብር)

ለREF ያልተለቀቀ የብድር መጠን(ብር)1

የተበዳሪ ማህበራት ቁጥር

355,219,797

187,192,357.49 15,518,856.60 168,,027,440 652

እ.ኤ.አ እስከ መስከረም 30 ቀን 2016 WEDP ፕሮግራም ሂሳብ ዝርዝር

እ.ኤ.አ እስከ መስከረም 30 ቀን 2016 MDRE&EEP ፕሮግራም ሂሳብ ዝርዝር

እ.ኤ.አ እስከ መስከረም 30 ቀን 2016 የገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም ሂሳብ ዝርዝር

Page 26: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et

Development Issues

22

IntroductionEnvironmental Impact Assessment (EIA) is a process of evaluating the likely environmental impacts of a proposed project or development considering consistent with socio-economic, cultural and human-health impacts, both beneficial and adverse. The purpose of environmental assessment is to recognize any environmental consequences early in project design. In this regard, to understand the role of environmental impact assessment, conceptual policy frameworks and principles of development banks is very essential.

Development banking is a type of financial intermediation to help the country to reach a higher and sustainable level of development that could be national, regional or international financial institution designed to provide medium and long term capital as well as technical support for productive investment. Development banks by their unique feature established to fill a gap left by undeveloped capital markets and the reluctance of other banks to offer long term financing.

There are three models of development banking, which include:

1. The policy banking model: whose capital is sourced from government.

2. The universal banking model: those provide long term finance plus advisory services through investment and whose capital is sourced from the international financial markets and from their own financial instrument; and

3. The standard banking model: this is another model which provides development finance though independent development banks whose capital is sourced from their own with little or no support from government;

The classification is mainly based on the source of capital to the banks which could be from government budget or from international market or from their own sources.

Development Bank of Ethiopia provides loans to commercial agriculture, manufacturing industries, agro processing, mining and extractive industries and currently it starts lease financing services to Small and Medium Enterprises using its own income as a major source of capital. Based on the above models, DBE can be classified as the standard banking model.

The major characteristic of the Bank is that it employs project appraisal as a means to determine the viability of the project submitted for financing. Project appraisal looks at the technical, financial, management, marketing, environmental and economic aspect of the projects. Thus, like all development banks, DBE has special concern to environmental protection.

Concepts and Principles of Environmental Impact Assessment (EIA)The concept of EIA is a systematic process used to identify, evaluate and mitigate the environmental effects of a proposed project prior to major decisions and commitments being made. It considers socio-economic as

Conceptual Policy Frameworks and Practices of DBE in EIA Implementation

Taye Tinti Guyassa (L.L.B., L.L.M.)

Page 27: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 23

well as environmental health effects as an integral part of the process.

The International Association for Impact Assessment (IAIA) classified EIA principles into two tiers, these are, basic and operating principles. Basic principles apply to assess stages of EIA and to strategic environmental assessment (SEA) of policy, plans and programs. The basic principles which include: purposive, rigorous, practical, relevant, cost-effective, efficient, focused, adaptive, participative, interdisciplinary, credible, integrated, transparent and systematic. Therefore, these basic principles of EIA should be considered in EIA application.

The other principles are operating principles. Operating principles describe how the basic principles should be applied to the main steps and specific activities of the EIA process. These principles emphasize that the EIA process should be applied: as early as possible in decision making and throughout the life cycle of the proposed activity; to all development proposals that may cause potentially significant effects; to bio-physical impacts and relevant socio-economic factors, including health, culture, lifestyle, age, and cumulative effects consistent with the concept

and principles of sustainable development; to provide for the involvement and impute of communities and industries affected by a proposal, as the interested public. These all have to be applied in accordance with internationally agreed measures and activities.

Development Bank of EthiopiaThe history of Development Bank of Ethiopia goes back to 1909 when the first attempts of its kind known as “The Society for the Promotion of Agriculture and Trade” was established during the Reign of Menelik II. In other words it has been long since the establishment of DBE with the purpose of promoting national development program.

The Bank’s area of focus is lending to viable projects in line with government priority areas. The very purpose of the Bank is to promote the national development agenda by mobilizing fund from internal and external sources. Another important behavior of the Bank is that, it strongly believes that its national objective can only be achieved through environmental protection and the overall socio economic development. This shows that the mission of DBE is equally

Page 28: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et

Development Issues

24

applied to environmental protection and socio economic development of the country.

Why DBE need to Implement Environmental Impact Assessment /EIA/?EIA helps to enforce environmental standards which can potentially induce promoters of the project to apply environmentally friendly production methods and practices. The Bank’s major environmental concern tends to be indirect which arises from the provision of financial services to business customers operating in sensitive sectors. It is believed that taking due account of environmental and social impacts is not only the right thing to do but also it makes the business itself the better performer.

In 1989, the World Bank adopted operational Directive (OD) 4:00 Annex A: environmental assessment and it became standard procedure for the Bank’s financed investment projects. The Bank requires environmental assessment (EA) of projects proposed for Bank financing to ensure that they are environmentally sound and sustainable, and thus to improve decision making. Hence, the purpose of operational Directive of the World Bank in making EIA of project as a requirement of lending is to guarantee the proposed activities have no negative effect on the environment.

Following the World Bank, African Development Bank /AfDB/ has also strong influence on the allocation of resources, and governance is an important factor in the assessment of country performance. The AfDB uses a tool called the Country Policy and Institutional Assessment (CPIA) designed to assess the quality of a country’s policy and institutional framework.

African Development Bank used EIA as a tool to assess the policy of that credit seeking country, its governance and institutional set up.

Similarly, the objective of EIA policy of DBE is to enforce the environmental policy of Ethiopia. This is because environmental sustainability is recognized in the FDRE constitution. The FDRE Constitution Article 92/3 says that the

design and implementation of programs and projects of development shall not damage or destroy environment. Thus, the main purpose of DBE to conduct EIA of projects financed by the Bank is to protect the harming effects of those projects.

The overall goal of environmental policy of Ethiopia is to enhance the environment as a whole to meet the needs of the present generation without compromising the ability of future generations to meet their own needs.

Thus, as a development bank, DBE should implement the Environmental Policy of Ethiopia on its part which has the goal to improve the health and quality life of all Ethiopian and to promote sustainable social and economic development and good governance. Therefore, the Bank itself should serve Government as a means of promoting good governance and sustainable development by applying environmental impact assessment of projects financed by it.

Environmental Impact Assessment Policy Frameworks of DBECredit Manual of Development Bank of Ethiopia (DBE) takes the environmental laws and regulations of the country to be respected as a requirement of loan processing. Hence, if the promoter designs the proposed project against the environmental laws of the country, DBE shall not finance the project.

According to its policy, when the proposed project is submitted to DBE, the Bank has to ensure that the project complies with all environmental laws and regulations including the constitutional environmental rights of the people. Therefore, to implement the stated requirements regarding environmental impact assessment, the Bank should be ensured that whether or not the proposed project could cope up with the laws and regulations of the country.

EIA Implementation Practice of DBE The major EIA mitigation measure as recommended in the project appraisal

Page 29: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 25

reports of DBE financed projects are timely collection and disposal of solid waste; effluent treatment; abating air, soil water and noise pollution as well as provision of protective wear to workers. Therefore, the follow up of EIA implementation should include the above basic elements.

Good opportunities and challenges while practicing EIA in DBEThere are good opportunities and challenges facing DBE to Implement Environmental Impact Assessment. DBE’s credit policy manual considers the environmental impact mitigation measures as eligible costs of project in appraisal process. Therefore, the project is financed together with the cost of environmental impact mitigation measures. In short, the promoter of the project is expected to implement the recommended EIA mitigation measures considering as part of the project cost which is financed by the Bank. This is good opportunity to implement EIA within DBE financed projects.

On the other hand, there are some challenges facing DBE while implementing EIA, which include, among others, absence of professional environmentalist who participate in the project screeining process as well as in making close follow up at the implementation of EIA requirements of DBE in general.

Conclusion

In general, environmental concerns are often trapped by economic development plans and external securities. The problem is keeping the development of industry and protection of environment in balance. Environmental impact Assessment norm is evolved to serve as powerful tools to balance these conflicting interests. As discussed above, to integrate environmental instruments is necessitated in the use of EIA as a legal regime to promote sustainable development agenda of international community. To achieve

its purpose, EIA implementation should consider the basic and operating principles, which include, among others, it must be implemented early and through the life cycle of the project and also be participative. In this regard, DBE has EIA policy framework and it has institutional capacity to convert EIA laws into practice.

On the other hand, DBE lacks some elements of EIA implementation mechanisms. These shortages are: lack of environmental working unit with relevant profession, lack of awareness, lack of adequate legal documents and also no means of communication with concerned government authority in EIA implementation process. Furthermore, there is no follow up, monitoring and evaluation practice of recommended EIA mitigation measures while the project is operating and /or there is no means of ensuring it. In practice, DBE requests approved EIA certificate to approve that the project is environmentally friendly. However, the Bank lacks practice of reviewing EIA reports and categorization of projects in accordance with their magnitude of environmental impact.

Therefore, to ensure the implementation of EIA of projects and to promote sustainable development policy of Ethiopia as a government tool it is important to recommend the following conditions: The implementation process of EIA need to have detailed Guidelines and Directives which should be specifically established for review of EIA report and screening of projects proposed for the Bank’s financing, monitoring and evaluation of compliance to the recommended EIA mitigation measures or any other newly detected environmental impact of DBE financed projects. Furthermore, standard format of follow-up report should be developed. By virtue of Public Enterprises Proclamation No. 25/1992, DBE would formulate its Guidelines and Directives through the approval of Board of Management (BOM). Therefore, to incorporate these legal documents, DBE should review its EIA policy and procedure.

Sources: FDRE Constitution, National Laws and Environmental Policy, DBE’s EIA Policy and Credit Policy Documents, International and Regional Environmental Conventions and Declarations, International Court of Justice Judgments, Observation, personal experience and Interviews made with DBE’s managers, and so on…

Page 30: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et

General Knowledge ጠቅላላ ዕውቀት

26

ብዙ ጊዜ የውጤታማ እና ስኬታማ ሰዎችን ታሪክ ብሎም የውጤታማነትን ምስጢር ማጥናት እና መተረክ ሌሎችን እንደሚያስተምር ይታመናል፡፡ ይህን መሰል ታሪክ ማወቁም ራስን ለስኬታማነት ለማዘጋጀት ከፍተኛ አስተዋፅዖ አለዉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የደካሞችን እና ስኬታማ መሆን ያልቻሉ ሰዎችን እና ስራ መሪዎችን ታሪክ ማጥናት እና መተረክ ራሱን የቻለ ጥቅም አለው፡፡ አንድ ሰው ባለበት ከፍተኛ የስራ ሃላፊነት/መሪነት/ ስኬታማ መሆን ያልቻለበት ወይም የሚመራውን ድርጅት ለውድቀት የዳረገበትን ምክንያት ማጥናት ሌሎች ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ እና የተሻለ መሪ ለመሆን እንዲችሉ ያግዛል፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ ከተለያዩ ፅሁፎች የተሰበሰቡ ሥኬታማ ያልሆኑ መሪዎች 10 መገለጫዎች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡

1. ለሁሉም መልስ አለኝ ማለት

በመሪነት የተመረጡት ከሌሎቹ በበለጠ የተሻሉ በመሆናቸው እና ማንም የእነሱን ያህል መሆን እንደማይችል የሚያስቡ በመሆናቸው በውሳኔዎቻቸው እና ችግር አፈታት ሂደታቸው ወቅት ሌሎችን ማሳተፍ ጥቅም እንደሌለው በማመን ሁሉም ጉዳይ ላይ ራሳቸው መልስ እና ውሳኔ መስጠትን ይመርጣሉ፡፡

እዚህ ላይ ልናስተውለው የሚገባ ጉዳይ አንድን ድርጅት ስንመራ ውሳኔዎች ፈፃሚዎችን ያማከለ/ያሳተፈ መሆኑ ትግበራ ላይ ያለውን አዎንታዊ ተጽዕኖ ነው፡፡ ሰራተኞችን በውሳኔዎች ላይ ባሳተፍን ቁጥር አዳዲስ አሰራሮችን ወደ ድርጅታችን በማስገባት የድርጅቱን የፈጠራ ክህሎት ማበልፀግ ብሎም የደንበኞችን ፍላጎት በተሻለ መልኩ ማርካት የሚያስችል እድል ያስገኛል፡፡

2.. ማውራትን ከመስራት ጋር ማመሳሰል

አንዳንድ ውጤታማ ያልሆኑ ስራ መሪዎች ማውራትን እና መስራትን አንድ አድርገው ያያሉ፤ አንድ ወቅት አንድ የስራ መሪ ‹‹ጥሩ እየሄደ ነው፤ላለፉት ሁለት ቀናት ስንወያይበት ነበር›› የሚል መልስ ለአለቃው እንደሰጠው አስታውሳለሁ፡፡ ከዚህ መረዳት እንደምንችለው የስራ መሪው በጉዳዩ ላይ ማውራቱን እንደ ስኬት ማስቀመጡን ነው፤ ዳሩ ግን በግማሽ ቀን የተግባር ስራ መፍትሄ ማግኘት የነበረበት ጉዳይ ለሁለት ቀናት መፍትሄ ሳያገኝ ቆይቷል፡፡ የዚህ አይነት የስራ መሪዎች ብዙውን ጊዜ ‹‹እንዲህ አድርጌ እሰራዋለሁ፣ እንዲህ አድርገን ልንሰራው ነው፣ እየተነጋገርንበት ነው›› የሚለውን መልስ ልክ ስራውን እንደሰሩት እንዲሰማቸው ስለሚያደርግ በተግባር ሥራ ላይ ውጤታማ አይሆኑም፡፡ በሀገርኛው አባባልም ‹‹የሚጮህ ውሻ አይናከስም›› እንዲሉ፡፡

3. ከመፍትሄ ይልቅ ወቀሳ ላይ ማተኮር

‹‹የማን ጥፋት እንደሆነ እንወቅና ሰውየውን በማባረር ይህን መሰል ጥፋት እንዳይደገም ማድረግ አለብን›› በሚል አስተሳሰብ የሚመሩ የስራ መሪዎች የችግሩን መንስዔ አጥንተው ቋሚ መፍትሄ ከመስጠት ይልቅ በወቅቱ ስራው ላይ የነበረውን ሰው በማባረር ችግሩ እንዳለ ለሌላ/ተተኪ/ ሰው ያስተላልፉለታል- ጉልቻ እንደመቀያየር አይነት፡፡

4. ቅጽበታዊ ስኬቶች ላይ ማተኮር

ብዙ ትናንሽ እና የአጭር ጊዜ ግቦች ወደ ረጅሙ ግብ እና ራዕይ ያደርሳሉ በሚል አመለካከት ብዙውን ጊዜ በጥቃቅን ስራዎች እና የአጭር ጊዜ ዓላማዎች ላይ ጊዜን በማጥፋት ዋናውን እና የረጅሙን ጊዜ ግብ ችላ ይሉታል፡፡ ይህም ጊዜን በጥቃቅን ጉዳዮች ከማባከኑም በላይ ትልቁን የድርጅት ዓላማ እስከመርሳትም ያደርሳል፡፡

5. ከጥንካሬ ይልቅ ድክመት ላይ ማተኮር

ስኬታማ ያልሆኑ የስራ መሪዎች ደካማ ጎናቸውን ሌሎች እንዳያውቁት እና ‹ደካሞች› እንዳይባሉ በማሰብ ብዙ ጊዜያቸውን የሚያጠፉት ድክመታቸውን ለመሸፈን በመጣር ወይም በመደበቅ ተግባር ላይ ነው፡፡ ይህ ሁኔታቸው ጥንካሬያቸው ላይ በማተኮር ብዙ የተሻለ እና ውጤታማ ስራ ሊያከናውኑ የሚችሉበትን ጊዜ እንዲያባክኑ ያደርጋቸዋል፡፡ ይህም ውጤታማነትን የሚያሳጣ ባህርይ መሆኑን ብዙ ጸሐፍት ተርከውታል፡፡

6. ጠንካራ ሠራተኞችን የማደናገር እና ማወዛገብ ሥራ ላይ መጠመድ

ጠንካራ እና ብርቱ የሆኑ ሰራተኞችን በሆነ ባልሆነው ነገር ላይ ሁሉ ትችት በመስጠትና በማስደንገጥ ባላቸው አቅም ሥራ ላይ እንዳያተኩሩ ማድረግ የእነዚህ ደካማ መሪዎች መገለጫ ነው፡፡ ‹‹አሸናፊዎች ዝም አይሉም፣ ዝምተኞች አያሸንፉም›› በሚል መርህ የሚመሩት እነዚህ መሪዎች የተሻለ ውጤት ማስገኘት የሚችሉ ሰራተኞቻቸውን ሞራል ከመገንባት ይልቅ እንዲደነጋገሩ እና እረፍት እንዲያጡ በማድረግ ውጤታማነታቸውን ዝቅ ከማድረግ ባለፈ የድርጅቱን ውድቀት ያፋጥኑታል፡፡

7. መሪን ማፍራት አለመቻል

በአንድ ስልጠና ላይ አንዲት አሰልጣኛችን ‹‹መሪ ማለት ተከታዮች ያሉት ሳይሆን መሪዎችን መፍጠር የሚችል ነው›› ማለቷን አስታውሳለሁ፡፡ ይህም አንድ ውጤታማ መሪ ሊሞገስ የሚገባው እርሱን የሚተኩ ተተኪ መሪዎችን መፍጠር እና ከነርሱ ጋር መስራት ሲችል መሆኑን ያስረዳናል፡፡ በተቃራኒው ደካማ መሪዎች ሌሎች ቦታቸውን የሚወስዱባቸው ያህል ስለሚሰማቸው የሰራተኞቻቸውን

አንተነህ መለሰ

ስኬታማ ያልሆኑ መሪዎች ልማድ10

(ወደ ገፅ 36 ዞሯል)

Page 31: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 27

የሥራ ላይ ጫና /Organizational Stress/ ማለት በአንድ ተቋም ከሥራ ጋር ተያያዥ በሆነ ምክንያት ሊከሰት የሚችል ሆኖ ተቋሙን ወይም ድርጅቱን ስጋት ላይ የሚጥል ችግር ነው፡፡ የሥራ ላይ ጫና እንደ ተቋሙ የሥራ ባህርይ ሊለያይ ቢችልም ሁሉም ተቋማት የሥራ ላይ ጫና ችግርን እንደሚያስተናግዱ ይታመናል፡፡ በአንድ ተቋም ላይ ይህን መሰል ችግር ሲከሰት በአፋጣኝ የችግሩን መንስኤ በመለየት መፍትሔ መፈለግ ካልተቻለ የተቋሙ ውጤታማነትና ምርታማነት ከመቀነሱም በላይ ተቋሙ በደንበኞች ዘንድ ያለው ተቀባይነትና አመኔታ እንዲጠፋ ያደርጋል፤ ይባስ ብሎም ተቋሙን ለከፍተኛ ኪሳራ ሊዳርገው ይችላል፡፡

የሥራ ላይ ጫና መነሻዎች

በአንድ ተቋም ውስጥ የሥራ ላይ ጫና እንዲፈጠር በምክንያትነት የሚቀመጡ በርካታ ጉዳዮች ቢኖሩም በዋነኝነት ግን በራሱ በተቋሙ እና በሠራተኛው ምክንያት የሚከሰቱ ናቸው፡፡ እነዚህም፡-

1. ተቋማዊ የስራ ላይ ጫና ምክንያቶች /Organization-al Stressors/፡- በተቋሙ ወይም ተቋሙ ለሠራተኞቹ በሚሰጠው ሥራ ምክንያት የሚከሰቱ ናቸው፡፡ እነዚህም፡

1.1. ከፍተኛ የሆነ የሥራ መደራረብ፡- ለሰራተኞች ከባድና ውስብስብ የሆኑ ስራዎችን በጣም አጭር በሆነ የጊዜ ሰሌዳ ውስጥ እንዲያጠናቅቁና ተደራራቢ ስራዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ሰርተው እንዲያቀርቡ ማስገደድ ሰራተኛው ላይ አላስፈላጊ ጭንቀት ከመፍጠሩም በላይ ሰራተኛው በስራው

እንዲሰላችና ስራውን በሚፈለገው የጥራት ደረጃ እንዳይሰራ ያደርጋል፡፡

1.2. በግልፅ የተቀመጠ የሥራ ኃላፊነት አለመኖር፡- ሰራተኞች በተቋሙ ውስጥ ያላቸውን ድርሻ በግልፅ እንዲያውቁት አለማድረግና ተጠሪነታቸው ለማን እንደሆነ በግልፅ እንዲያውቁት አለማድረግ ለሚሰሩ ስራዎች ወይም ለሚፈጠሩ ስህተቶች ሃላፊነቱን የሚወስድ አካል እንዳይኖር ያደርጋል፡፡ ሰራተኞች ካላቸው የትምህርት ዝግጁነትና ከያዙት የስራ ልምድ እጅግ የራቀ ስራን በሃላፊነት እንዲሰሩ ማስገደድ፡፡

1.3. ለሠራተኞች ምቹ የሆነ የሥራ ቦታ አለመፈጠር፡- ማንኛውም ሠራተኛ የሥራ ባህርይ አስገዳጅ ካልሆነበት በስተቀር ንፁህ፣ ምቹና ከአደጋ ሥጋት ነፃ በሆነ ቦታ የመሥራት መብት አለው፡፡ ተቋማትም ለሥራቸው ጥራትና ውጤታማነት እንደሚጨነቁት ሁሉ ሥራውን ለሚሰሩላቸው ሠራተኞች ጥሩ የሆነ የሥራ ቦታ እንዲያመቻቹ ይገደዳሉ፡፡ ሆኖም ግን በማንኛውም ምክንያት ለሠራተኞች ምቹ ያልሆነ የሥራ ቦታ ሲያጋጥም ሠራተኞች ላይ የሚፈጠረው ጭንቀትና የሥራ ቦታን የመጥላት ስሜት የተቋሙን ህልውና ስጋት ላይ እንዲወድቅ ያደርገዋል፡፡

1.4. የተቋሙ ፖሊሲ፡- በየጊዜው የሚለዋወጥና ወጥ ያልሆነ እንዲሁም ሠራተኞች በግልፅ እንዲያውቁት የማይደረግ ፖሊሲ መኖር ሠራተኞች ተቋማቸውን በሚመለከት አንድ ወጥ የሆነ አቋም እንዳይኖራቸው ያደርጋል፡፡

ስምምነት ከበደ

የሥራ ላይ ጫና ምንድነው?

Page 32: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et

General Knowledge ጠቅላላ ዕውቀት

28

2. ውጫዊ የሥራ ላይ ጫና ምክንያቶች /External Organi-zational Stressors/፡- በውጫዊ ምክንያትነት የሚጠቀሱት በግለሰብ ወይም በሠራተኛው ምክንያት የሚከሰቱ ችግሮች ሲሆኑ እነዚህም ፡-

2.1. የአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች መፈጠር፡- በከፍተኛ ፍጥነት እየተሻሻሉ ከሚመጡት የቴክኖሎጂ ውጤቶች ጋር እኩል መጓዝ አለመቻል፡፡

2.2. በሥራ ምክንያት ከቤተሰብ መራቅ፡- ሰዎች ከሚሰሩበት ተቋም የሥራ ባህርይ የተነሳ ለአጭር ወይም ለረጅም ጊዜ ከቤተሰባቸው ተለይተው እንዲሰሩ ሲደረጉ ከቤተሰባቸው መራቃቸው የሚፈጥርባቸው ችግር በቀጥታም ባይሆን በተዘዋዋሪ ሥራቸው ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ መኖር፡፡

2.3. በተፈጥሮ ወይም በሰው ሰራሽ አደጋዎች ምክንያት የሚፈጠሩ ችግሮች፡- በፆታ፣ በዘር፣ በኃይማኖትና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች በሚፈጠሩ ማኅበራዊ ቀውሶች ምክንያት ሰዎች ሥራቸውን በአግባቡ እንዳይሰሩ ወይም የሥራ ቦታቸውን እንዲጠሉ የሚያደርጉ ተግዳሮቶች በዋነኝነት ይጠቀሳሉ፡፡

3. ግለሰባዊ የሥራ ላይ ጫና ምክንያቶች / Individual Stressors/:- በአንድ ተቋም ውስጥ የተለያዩ ሠራተኞች እንደመኖራቸው መጠን በተቋሙ ላይ ለሚፈጠረው ጫና የሚኖራቸው አስተዋጽዖም የዚያኑ ያህል ይለያያል፡፡ በአንድ ተቋም በግለሰብ ደረጃ ጫና ሊያሳድሩ የሚችሉ ምክንያቶች ፡-

3.1 ኃላፊነትን በአግባቡ መወጣት አለመቻል፡- ሠራተኞች የተጣለባቸውን ኃላፊነት ከዕውቀት ወይም ከችሎታ ማነስ ወይም በሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች የተነሳ መወጣት ካልቻሉ እንዲሁም አብረዋቸው ከሚሰሩ ሠራተኞች ጋር ጥሩ የሆነ የሥራ ግንኙነትና የልምድ ልውውጥ አለመኖር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተቋሙ ላይ ለሚፈጠረው የሥጋት ጫና አስተዋፅዖ ይኖረዋል፡፡

3.2. የሠራተኛው /የግለሰቡ/ ግላዊ ባህርይ፡- በየትኛውም ተቋም ውስጥ የሥራ ተነሳሽነታቸው ከፍተኛ የሆነ፣ የሚሰሩበት ተቋም ዓላማ ጠንቅቀው የሚያውቁና ዓላማውን ከግብ ለማድረስ የሚጠበቅባቸውን ሁሉ ከማድረግ ወደኋላ የማይሉ ሠራተኞች እንዳሉ ሁሉ በጣም ስልቹ፣ ቁጡና የሚሰሩበትን ተቋም ዓላማ ጠንቅቀው የማያውቁ ለሚሰሩበት ተቋም ደንበኞች ወይም ተገልጋዮች የቅሬታ ምንጭ የሆኑ ሠራተኞች በተቋሙ ውስጥ መፈጠር ተቋሙን ለአደጋ ያጋልጠዋል፡፡

4. የሥራ ላይ ጫና በሰራተኛው ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ • ሥራን በትኩረት ለማከናወን አለመቻል • የውሳኔ ሰው ለመሆን መቸገር • የሥራ ተነሳሽነት መቀነስ • በሥራ የመደሰት ስሜትን መቀነስ • የመድከምና የመደበር ስሜት መሰማት • የእንቅልፍ ማጣት ችግር • እንዲሁም ለተለያዩ የጤና ችግሮች መጋለጥ ናቸው።

5. የሥራ ላይ ጫና በተቋሙ ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ • ከስራ ገበታቸው ላይ የሚቀሩ ሠራተኞች ቁጥር መጨመር

• የሥራ ተነሳሽነት መቀነስ • ሥራ የሚለቁ ሠራተኞች ቁጥር መብዛት

• የሥራ ብቃትና ውጤታማነትን መቀነስ • ሥራ ላይ ቸልተኛ የሚሆኑ ሠራተኞች ቁጥር መበራከት

• በተቋሙ ላይ ከደንበኞች ተደጋጋሚ የሆነ ቅሬታ መቅረብ

• የተቋሙን መልካም ገጽታ የሚያበላሹ ድርጊቶችን የሚፈፅሙ ሠራተኞች ቁጥር መበራከት እና የመሳሰሉት ናቸው።

6. የሥራ ላይ ጫናን መከላከያ መንገዶች

6.1. የመጀመሪያ ደረጃ መከላከያ /Primary Prevention/ • ሠራተኞች የስራ ድርሻቸውንና ኃላፊነታቸውን በግልፅ እንዲያውቁት ማድረግ

• የሚሰጡት ሥራዎች በተቻለ አቅም ከሠራተኛው ችሎታና እውቀት ጋር የተመጣጠነ እንዲሆን ማድረግ

• ሥራቸውን በተመለከተ ሠራተኞች የውሳኔ ሰጪነት ሚና እንዲኖራቸው ማድረግ

• ለሠራተኞች ምቹ የሆነ የስራ አካባቢን መፍጠር • በሠራተኞችና በኃላፊዎች መካከል ጥሩ የሆነ የሥራ ግንኙነት እንዲኖር ማድረግ

• እንደ አስፈላጊነቱ ተቋማዊ የፖሊሲ እና አስተዳደራዊ ለውጦችን ማድረግ

• የሚሰሩበት ተቋም መኖር ለእነርሱ እንደሚያስፈልግ ሁሉ ሠራተኞችም ለሚሰሩበት ተቋም አስፈልገዋለሁ በሚል ስሜት ጥሩ የሆነ ራስን የመምራት ባህርይ በማዳበር በሥራቸው ውጤታማ እንዲሆኑ መጣር፡፡

• ሠራተኞችን ለጭንቀት የሚዳርጉና ሥራን በአግባቡ ለመሥራት የሚያውኩ ነገሮችን መቆጣጠርና መከላከል መቻል

• በተቻለ አቅም በተቋሙ ውስጥ ትጉህ ለሆኑ ሠራተኞች እውቅና በመስጠት በሠሩት ሥራ ምስጋናና ተገቢውን አክብሮትን እንዲያገኙ በማድረግ የሌሎች ሠራተኞችን የሥራ ተነሳሽነት ማሳደግ እንዲሁም ጤናማ የሆነ የፉክክር መንፈስ እንዲኖር ማድረግ

6.2. ሁለተኛ ደረጃ መከላከያ /Secondary Prevention/ • በሠራተኞች መካከል የፉክክርና የቡድን ሥራ መንፈስ እንዲኖር ማበረታታት

• ጥናቶችን በማካሄድ የተለያዩ ፕሮግራሞችን መዘርጋት • ሠራተኞችን ማብቃት የሚያስችሉ ሥልጠናዎችና የትምህርት ዕድሎችን ማመቻቸት

• የሥራ ላይ ሥልጠና መስጠት • ሠራተኞች ከሥራ ጋር ተያያዥ የሆኑ የትምህርት ዕድሎችን እንዲያገኙ ማድረግ

• በሠራተኞች መካከል ጠንካራ የሆነ ማኅበራዊ ግንኙነትን እንዲኖር ማድረግ

6.3. ሶስተኛ ደረጃ መከላከያ /Tertiary Prevention/ • ሠራተኞችን መደገፍና ማገዝ • ጠንካራ የሆነና ኃላፊነት የሚሰማው አስተዳደራዊ ሥርዓት መዘርጋት

• ሠራተኞችን የማገዝ/ የማብቃት ፕሮግራሞችን መንደፍ

• በግል ችግር ምክንያት ሥራቸውን ለመሥራት የተቸገሩ፣ በሥራ ቦታ የመሰላቸት ወይም የመደበት ስሜት የሚሰማቸው ሠራተኞች ካሉ የስነልቦና ባለሙያ

Page 33: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 29

Different steps have been undertaken for the Implementation of Enterprise Resource Planning (ERP) System beginning from the signing of Service Contract Agreement on July 27, 2016 held between Development Bank of Ethiopia and an Indian based Company, Tech Mahindra Ltd (TechM).

The objective of the agreement was to enhance the operational efficiency of the Bank’s business resources in order to achieve its strategic objectives. The agreement comprises training programs, customization and implementation of ERP to the Bank.

Following the agreement, the Bank had kicked off an Enterprise Resource Planning (ERP) System Project on Monday, October 10, 2016 with presentation and discussion.

As per the schedule, the contract agreement held between DBE and (TechM) will be completed in the coming few months of time.

For the successful completion of the Project, the Bank had established a dedicated ERP Project Management Office led by a Project

Manager, Business and Technical Managers with 32 members, having adequate exposure for the successful completion of the Project.

Besides, the implementer company, Tech Mahindra Ltd, introduced Indian consultants assigned to work for the Project. Furthermore, the expertise had broad exposure and they will manage the Project implementation pertinent to the Bank’s expectation.

DBE ERP Project implementation project covers 13 modules which include six Financial, four Human Resource Management and three Property Management modules, and the project also cover building a dataware house and business intelligence tool for report generation.

Since then, the Bank is paid close follow-up on the implementation of the Project which has to be completed as per the schedule.

TechM is a platinum partner of Oracle systems Ltd which is Oracle ERP System Vendor responsible for implementing, customizing and giving training as per the Bank’s acquires.

ምክር እንዲያገኙ ማድረግ • ሠራተኞችን ለጭንቀት እንዲሁም ሥራቸውንም ሆነ የሚሰሩበትን ተቋም እንዲጠሉ የሚያደርጉ ድርጊቶች ወይም አሰራሮች እንዳይኖሩ ማድረግ

በአጠቃላይ አንድ ተቋም ከላይ ከተዘረዘሩት ችግሮች ሙሉ በሙሉ ነፃ እንዲሆን ማድረግ ባይቻልም በተቻለ አቅም ግን ችግሮቹንና የሚያስከትሉትን ጉዳት ግን መቀነስ ይቻላል፡፡

በማንኛውም የስራ ዘርፍ የተሰማራ ተቋም ውጤታማ የሆነ ሥራ በመሥራት ራዕዩን ለማሳካት ሲጥር ጎን ለጎን ለውጤታማነቱ እንቅፋት የሚሆኑ ችግሮች በመለየት አስፈላጊ ከሆነም ተከታታይነት ያለው ጥናት በማካሄድ ለችግሮቹ መፍትሔ መስጠት ይኖርበታል፡፡

ይህን ማድረግ የተቋሙ የበላይ ኃላፊዎች የሰራተኞችን

ፍላጎት በመረዳትና ለውጥ የሚያመጡ አሰራሮችን በመዘርጋት ረገድ ከፍተኛውን ኃላፊነቱን የሚወስዱ ሲሆን ሌሎች የተቋሙ ሠራተኞችም ባላቸው የሥራ ድርሻና በተሰጣቸው ኃላፊነት ልክ የመፍትሔው ዋነኛ አካል መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡

በዚህ ረገድ በተለያዩ ክፍሎች የሚሰሩ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ለተቋማቸው ተመሳሳይ የሆነ አቋም በመያዝ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ሲፈጠሩ በመነጋገርና በመረዳዳት መፍትሔ የመስጠት ልምድ ሊያዳብሩ ይገባል፡፡ በተለይም በሠራተኞችና በየደረጃው በሚገኙ የሥራ ኃላፊዎች መካከል ጥሩ የሆነ ተግባቦት እንዲኖር ማድረግ በተቋማት ላይ የሚፈጠረውን የሥራ ላይ ጫና /Organizational Stress/ በመቅረፍ ተቋሙን ከሚጋረጥበት አደጋ መታደግ ይቻላል፡፡

Reference: Habtamu Wondimu (Prof.) and Dawit Mekonnen (Phd). August, 2014. Group and Organizational Dynamics Module. Addis Ababa University College of Social Sciences. Addis Ababa. Ethiopia.

The Status of DBE’s ERP System Implementation

Page 34: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et

General Knowledge ጠቅላላ ዕውቀት

30

The One Minute Manager is a short book by Ken Blanchard and Spencer Johnson. The brief volume tells a story, recounting three techniques of an effective manager: one-minute goals, one-minute praisings and one-minute reprimands. Each of these takes only a minute but is purportedly of lasting benefit.

In this regard, The One Minute Manager Book will provide insights for those managers who are working at any company operating across the world in general and financial institutions in Ethiopia in particular such as Development Bank of Ethiopia. The Book will also give an opportunity for managers who enable to exercise their leadership role at their day-to-day activities in achieving set goals. The Book, since it was first published in 1982, has been sold more than 13 million copies with 37 languages. The One minute manager is not simply a book for managers basically it has brilliant strategy on the ways how to effectively and efficiently work with employees. Thus, before I jump to the book

I prefer to catch the powerful messages of the author “If you haven't read it, do . . . if you have, read it again.".

As mentioned above, the Book has over 100 pages with three major topics. These are:

One Minute Goal Setting is the first secret and the foundation for One Minute Management. The authors advocate the 80-20 goal-setting rule: that 80% of your really important results will come from 20% of your goals. How do you get people truly excited about their work? Make it clear what is expected from them. One Minute Goal Setting is simply:

1. Agree on your goals.

2. See what good behavior looks like.

3. Write out each of your goals on a single sheet of paper using less than 250 words.

4. Read and re-read each goal, which requires only a minute or so each time you do it.

Fantahun Tilahun (BSC in Computer Science, MBA in Project Management)

The One Minute Manager

Page 35: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 31

5. Take a minute every once in a while out of your day to look at your performance, and

6. See whether or not your behavior matches your goal.

One Minute Praising’s is the second secret. The authors suggest that effective managers help people reach their full potential by catching them doing something right. "People who feel good about themselves produce good results." The One Minute Praising works well when you:

1. Tell people up front that you are going to let them know how they are doing.

2. Praise people immediately.

3. Tell people what they did right - be specific.

4. Tell people how good you feel about what they did right, and how it helps the organization and the other people who work there.

5. Stop for a moment of silence to let them "feel" how good you feel.

6. Encourage them to do more of the same.

7. Shake hands or touch people in a way that makes it clear that you support their success in the organization.

One Minute Reprimand is the third and final secret to effective managing. "Clearly the number one motivator of people is feedback on results." Feedback is the breakfast of champions. The One Minute Reprimand works well when you:

1. Tell people beforehand that you are going to let them know how they are doing and in no uncertain terms.

The first half of the reprimand:

2. Reprimand them immediately. [Reprimand the behavior only, not the person or their worth]

3. Tell people what they did wrong - be specific.

4. Tell people how you feel about what they did wrong.

5. Stop for a few seconds of uncomfortable silence to let them feel how you feel.

The second half of the reprimand:

6. Shake hands, or touch them in a way that lets them know you are honestly on their side.

7. Remind them how much you value them.

8. Reaffirm that you think well of them but not of their performance in this situation.

9. Realize that when the reprimand is over, it's over.

The authors write that, as a manager, there are three choices when it comes to getting the most out of an employee:

1. Hire a winner (can be hard to find and expensive to hire and keep)

2. Hire someone with potential to be a winner and then systematically train them

3. Prayer

They suggest that option 2 is best. However, isn't it ironic that most companies spend 50-70% of their money on people's salaries and yet they spend less than 1% of their budget to train their people?

It has been said that "The best minute I spend is the one I invest in people." Effective managers manage themselves and the people they work with so that both the organization and the people profit from their presence. So, in summary, how can you give yourself and others "the gift" of getting greater results in less time? 1) Set goals; 2) Praise and reprimand behaviors; 3) Encourage people; 4) Speak the truth; 5) Laugh, work, enjoy!

"Everyone is a potential winner. Some people are disguised as losers...don't let their appearance fool you."

Page 36: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 32

organization has its own objectives for existence

and operates based on its plan using the resources available. Organizations have different resources such as human resources, financial resources, physical resources, and information resources. Of these resources, the Human Resources play a vital role in getting the planned tasks done. Organizations hire and pay employees for their time and competencies and here lies the importance of managing time effectively in order to enhance organizational affectivities.

Time is a crucial organizational resource and an important one that plays a noticeable role in boosting effectiveness and profitability in an organization. So, as a worker and leader of an organization, we should get time to talk about how we are managing our time in the work place.

The Nature of TimeIn order to understand time as a resource, it will be better to deal with its nature/characteristics. Let’s think that each day your bank deposits USD 86,400 in your checking account and there’s just one catch. You have to spend it all in one day. You can’t carry over any money to the next day. How could you spend the money? I had used this illustration in different training sessions. People have their own responses. But what we will see

here is the 86,400 seconds we are given each day for free.

• Time is neutral and a resource for free: we do not pay for the time we are given just it a natural resource equally given for everybody.

• Time is a Non Renewable Resource: we cannot renew time like the other natural resources.

• Time cannot be saved for future use: like money or other material resource, we cannot keep time for future use.

• Each activity requires a minimum quantum of time: in performing tasks, we are using time. Where we walk or work it always needs some amount of time as an input.

• Time has a value like currency: to realize the value of time, just think of a passenger missing his flight for a minute lateness.

To sum up, Time is free, but it's priceless. We can't own it, but we can use it. We can't keep it, but we can spend it. Once we've lost it, we can never get it back.

Managing Time Steven Covey in his book entitled “First Things First” suggests that time management is actually personal management – managing ourselves rather than managing time. The essence of time management is to organize and execute around priorities. Frankly

By: Anteneh Melese (MA in HRM)

Time: The Unnoticed Resource

Every

General Knowledge ጠቅላላ ዕውቀት

Page 37: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 33

speaking, we cannot manage time but ourselves. Time management is all about managing the events in life in relation to time. We may often wish for more time but we only get 24 hours, 1,440 minutes or 86,400 seconds each day. This makes time management difficult and calls for the skills learned through self-analysis, planning, evaluation, and self-control.

Why We Manage Time? • We are discussing about time

management because it is limited we should aim to:

• achieve more in the time available and get greater satisfaction from it

• increase productivity or output, which is a key issue in the assessment of people at work

• achieve organizational and personal goals • reduce time wasted • make the best use of high energy time • overcome bad habits • reduce pressure and stress, through

planning and • be economical, TIME IS MONEY.

How Can We Manage Time?In managing time, the first thing to be considered is the understanding of the time thieves and attempted them. Mismanaging time means wasting it for a non value adding activity. Thus, we will see the time thieves.

Unclear Objectives: People with a clear aim will attain what they want and the first time killer is failing to have a clear objectives. This works also for organizations. Managers in organizations need to have a clear objective and assign to employees in order to avoid the “what shall I do today” thought of employees.

Disorganization: It’s easy to see when your desk is too messy, but sometimes you have to step back and ask yourself if you are taking an organized approach in completing all of your tasks.

Interruptions: Have you ever noticed how individuals visited you today? Or the calls you answered while you were in the middle of doing something important? These visitors or calls can not only take you away from your

task, but sometimes they interrupt your train of thought and you can’t return to where you were without retracing your steps. For a visitor it may take 10 or 20 minutes but guess how much time you will lose if you had 10 visitors a day.

Telephone: It is clear that telephone and emails help us to facilitate our jobs. But they are also the major time thieves if not managed properly.

Too many things at once: Trying to perform many things at once will make us in active and kill our time just by jumping here and there.

Inability to say “NO”: There is always another person. Don’t accept all tasks.

More Interruptions: We all like to visit with others, but conversations at inappropriate times can cost us time when we have to stop what we are doing and redirect ourselves from our plans

Periods of Inactivity: As much as we think we are busy, there are times in our day when we are not really doing anything. Recognizing and making use of these times can have a positive effect on our efforts.

More or less, these are the major time wasters and time management starts with identification of which time thieves are visiting us. Once we understand the time wasters, it will be easy to design and implement effective strategies for managing time.

Strategies:Get Organized: Most people find that disorganization results in poor time management. Professional organizers recommend that you first get rid of the clutter. A frequently used method is to set up three boxes (or corners of a room) labeled “Keep” – “Give Away” – “Toss.” Separate the clutter by sorting items into these boxes. Immediately discard items in your “Toss” box. Your “Give Away” box may include items you want to sell, delegate, or discontinue so find a method to eliminate these items such as a yard sale, charitable donation, or gifts to friends or family members outside your home. With the

Page 38: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et

General Knowledge ጠቅላላ ዕውቀት

34

clutter gone, the next step is to implement a system that allows you to handle information (example: tasks, papers, e-mail, etc.) less, only once, when possible.

Prioritize: We cannot do all things at a time and we need to think of “First things First”. People usually spend engaged urgent but less important issues. To avoid such problem, it is better to understand and define what is important for us and their urgency give priority for issues urgent and very important, important not urgent, urgent but less important and less important and not urgent accordingly. This will help in focusing what is important for us and use our time in a fruitful manner.

Avoid Procrastination: There are some popular saying we should kept in my mind such as ''Never put off 'til tomorrow what you can do today" and “Job fills the available gap in time”. This indicated that we can perform a simple task within a day, a week or a month depending on the time we think we have. When we are taking long for doing such tasks we are procrastinating. Some people procrastinate because they simply do not want to do the job. The job could be as simple as filing a stack of papers or more complex such as fear of failure, lack of adequate information for the task, or bad habits. As workers, we procrastinate saying “we can make it tomorrow or some other day”. But it is wrong habit and unacceptable by any conditions and preconditions.

Delegate Others: Since we cannot do all the tasks by ourselves, it is important to think of delegating other for part of the tasks.

Delegation means assigning responsibility for a task to someone else, freeing up some of your time for tasks that require your expertise. Most managers spend their time trying to accomplish all the tasks that could rather be done by employees due to many reasons.

Learn to Say “NO”: There is always another person who can perform things that you cannot due to reasons and also we can perform a thing at a time. Hence, it is better to say NO than promising what you cannot perform. These NOs are called “Gentle NOs”. Saying no will save our time in many ways like stopping interruptions, avoid being overloaded.

Stop external time wasters: Visitors and interrupters are the major time wasters. Hence, we should have strategies for such interrupters. I had a colleague who sometimes locks his office when there is a need to be focused. Likewise, we may need to disable our phone to manage interruptions. Since the nature of the interrupters defer we cannot have the same suggestion for all but we can have a means to minimize them.

In conclusion, Time, having a distinct nature, has been a challenge for management. It is not managed like other resources because it is all about managing ourselves. In managing time, we should use a technique and system that works for us since no all time management tool works for everybody. It depends on who we are and the task we have.

Please let us start it with the simplest techniques now because we should start managing

References • Brian Tracy, Eat That Frog! 21 Great Ways to Stop Procrastinating and Get More Done in Less

Time, 2007, Barretee-Koehler Publishers Inc. • Laverne Forest and Sheila Mulcahy, First Things First, A Handbook of Priority Setting in Extension,

1976, University of Wisconsin- Extension, Division of Program and Staff Development • Patrick Forsyth, 100 Great Time Management Ideas from successful executives and managers

around the world, 2009, Marshall Cavendish International • Stephen Covey, et al, First Things First: To Live, to Love, to Learn, to Leave a Legacy, 1994, New

York: Simon and Schuster.

Page 39: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 35

በካዛንቺስ ታክሲ ውስጥ ከ4 ኪሎ ወደ ቢሮ እየመጣሁ ነው፡፡ ልክ ቤተ መንግሥት ስንደርስ አንዲት ከኋላ ወንበር የተቀመጠች ወጣት ‹‹ገብርኤል ጫፍ ወራጅ አለ እንዳታሳልፈኝ›› አለች፡፡ ከዚያ ሦስተኛ ወንበር ላይ የተቀመጠ አንድ ጠብደል ዘወር ብሎ ልጅቱን እንደመገላመጥ አድርጎ ‹‹ቀስ ብለሽ አትናገሪም? ምን ግማሽ መንገድ ሳንሄድ ያስጮህሻል? ሲጀመር እኔም ከዚሁ ገብርኤል ጋ ስለምወርድ ያንች መናገር አያስፈልግም ነበር፡፡ ከፊት የተቀመጥሁት እኔ እያለሁ አንች ከኋላ ሆነሽ መጮህሽ ምን ይሉታል?›› እያለ ይጮህባት ጀመር፡፡

እርሷም... ‹‹እንዴ? አንተ ከዚህ እንደምትወርድ በምን አውቃለሁና ነው አንተ ‹ወራጅ አለ› እስከምትል የምጠብቀው? ደግሞስ እኔ አፍ እያለኝ ያንተን መናገር መጠበቅ አለብኝ?›› አለችው ፈርጠም ብላ፡፡

ሰውዬ ሊያፍር ነው? ባሰበት፡፡

‹‹ዝም በይ ባክሽሽ... ለፍላፊ! የአሁን ዘመን ሴቶች ደግሞ መብታችሁና እኩልነታችሁ የሚታያችሁ ታክሲ ውስጥ ነው፡፡ ሁሉን ነገር ቅድሚያ ስንሰጣችሁ ጊዜ ምላሳችሁ ረዘመ፡፡ በየስብሰባው የምትናገሩት እናንተ ናችሁ፡፡ በየካፌው፣ በየፊልም ቤቱ፣ በየአደባባዩ የምትታዩት እናንተ ናችሁ፡፡ ሁሉንም ዝም ብንላችሁ ጭራሽ ታክሲ ውስጥ ‹ወራጅ አለ› ለማለትም አትቅደሙን አላችሁ፡፡ ቀድሞ መናገር ስለለመደባችሁ በቃ ገና ታክሲው ሳይንቀሳቀስ.... ‹እዚህ ጋ ወራጅ አለ... እዚያ ጋ እንድታወርደኝ...› ትላላችሁ፡፡ ቆይ የት ሄደን እንኑር? ምናለ ረጋ ብትሉ?....›› በቃ እንደወረደ ወረደባት፡፡

ሁላችንም በግርምት እያዳመጥን ነው፡፡ ልጅቱ ግራ በመጋባት ‹‹ህምም... ሰውዬው ጤና የለህም እንዴ? አሁን ስለመብት ማን አነሳ? ነገሩን የፖለቲካ ክርክር አስመሰልከው እኮ ! ችግር አለብህ እንዴ? ሆሆ!›› ስትለው ሰውየው እንደገና ብሶበት አረፈው፡፡ ቁጣውንም ንግግሩንም ጨመረበት፡፡

‹‹ጭራሽ ከፖለቲካ ጋር ታያይዥኛለሽ? አንድ ነገር በተናገሯችሁ ቁጥር ለክስ ሆነ እኮ ሩጫችሁ - የዘመኑ ሴቶች፡፡ እኔን ከፖለቲካ ጋር አታያይዥኝ እሺ... ልኑርበት፡፡ በሴት የተነሳ ራሴን ላጥፋ እንዴ? ለእናንተ ስል የት ሄጄ ልኑር? ደግሞ ‹ችግር አለብህ› ትያለሽ? እናንተ እያላችሁ ችግር የት ሊጠፋ? በሁሉም ቦታ ለእኛ ችግር መሆን ሆነ ስራችሁ፡፡ በሁሉም ቦታ ቅድሚያ ለእናንተ እተባለ እኛ ከችግር እንዴት እንውጣ?....›› ታክሲውን በአንድ ጎማው አቆመው ማለት ይቻላል፡፡

‹‹ኧረ ወራጅ... ወራጅ! ወራጅ!...›› አሁን እኔ ነኝ የጮሁት፡

፡ ልክ ገብርኤል ጫፍ ስንደርስ ልጅቱን ቀድሜ ወርጄ ከታክሲው ሸሸሁ፡፡ እንዴዴዴ... ነገሩ ከስድድብ ወደ ድብድብ ቢቀየርስ? ቢያንስ ምስክር ተብዬ ፖሊስ ጣቢያ ልውልም አይደል፡፡ ሙልጭ - እንዳላዬ፡፡

...

በልቤ ‹‹እርግጠኛ ነኝ ይሄንን ሰውዬ ከሰሞኑ ሚስቱና ውሽሞቹ እንዲሁም ጓደኞቻቸው ተደራጅተው ፍርድ ቤት ገትረውት ሀብትና ንብረቱንም አስፈርደውበታል፡፡ እንዲያ ባይሆን ይሄን የመሰለ ጠብደል በጠራራ ፀሐይ የቀትር ጋኔን እንደመታው ሁሉ ነገር እየፈለገ አይሳደብም ነበር፡፡ ወይኔ ምስኪን.... ሆድ ቢብሰው ነው››........ እያልሁ ስጓዝ ከኋላዬ ‹‹ወይኔ ምስኪን... ያ የቤት ጣጣው ለዚህ አበቃው ማለት ነው?›› የሚል ድምጽ ሰማሁ፡፡ ታክሲ ውስጥ አብራን የነበረች ሴትዮ ናት፡፡

‹‹ይቅርታ... ይሄንን ሰውዬ ታውቂዋለሽ እንዴ?›› ጠየቅኋት፡፡

‹‹አዎ! አውቀዋለሁ፡፡ የሥራ ባልደረባዬ ነበር›› መለሰችልኝ፡፡

‹‹ነበር? አሁንስ?›› ጥያቄዬን አከታተልሁ፡፡

‹‹ታሪኩ ብዙ ነው ባክህ፡፡ ከ4 ዓመት በፊት እኔ ከምሠራበት የግል ድርጅት ውስጥ ተቀጥሮ ይሠራ ነበር፡፡ ጎበዝና ታታሪ ባለሙያ ነበር፡፡ በወቅቱ ከቤተሰቡ ጋር በተፈጠረበት ችግር ምክንያት ከሥራ መቅረት አበዛህ ብላ የድርጅቱ ባለቤት ከሥራ አባረረችው፡፡ ከሥራ እንደተባረረም ሚስቱ ያለችውን ንብረት ተካፍላ ወጣች፣ ማለቴ ተፋቱ፡፡ የገጠመውን ችግር ሁሉ ለድርጅቱ አሳውቆና ለተፈጠረው የሥራ ክፍተት ይቅርታ ጠይቆ መልሱኝ ቢልም የሚሰማው አጣ፡፡ በሌሎች ድርጅቶች ከአንድም ሁለት ሦስት ጊዜ ቢቀጠርም በቤቱ የተረጋጋ ሕይወት ስለሌለውና ችግሩን ተረድቶ የሚያረጋጋው ስላላገኘ እንዲሁ ሥራ መቀያየር ብቻ ሆነ ኑሮው፡፡ ያው እንደምታየው በየሄደበት ካገኘው ሰው ሁሉ ጋር ይጨቃጨቃል፡፡ ሲያሳዝን....›› አለች ዓይኗ እምባ እያቀረረ፡፡

እውነትም ያሳዝናል፡፡ ያኔ በቀላሉ መስተካከል የሚችለው ችግሩን የሚረዳው በማጣቱ ለዚህ መብቃቱ ያሳዝናል፡፡

...

እንደሥነ-ልቦና (ሳይኮሎጂ) ባለሙያዎች ድምዳሜ ከሆነ ሰዎች ብዙውን ጊዜ በውጭ (በሥራ ቦታም ሆነ በማንኛውም የእርስ በርስ ግንኙነት) የሚያሳዩት ባሕርይ የቤት ውስጥ

መላኩ አላምረው

“የቤትህን አመል እዛው...” ከማለት ባሻገር!

Page 40: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et

General Knowledge ጠቅላላ ዕውቀት

36

አጠቃላይ ሁኔታ ነፀብራቅ ነው፡፡ በቤቱ ሰላም የሌለው በውጭም ሰላም ያጣል፡፡ ቤቱ በደስታ የተሞላለት እድለኛ ደግሞ በየሄደበት ደስተኛ ሆኖ ይውላል፡፡ ለሰዎችም የደስታ ምንጭ ይሆናል፡፡ ቤቱ ሰላም-አልባ የሆነበት ደግሞ ውሎው ሁሉ ሰላም ይርቀዋል፡፡ የሌሎችንም ሰላም መረበሹ አይቀርም፡፡

የዚህ ሥነ-ልቦናዊ አተያይ ግልባጭም እውነት ነው፡፡ የሥራ ቦታውና አካባቢው ነባራዊ ሁኔታ ለቤቱ ይተርፋል፡፡ በሰላማዊ አካባቢ የዋለ ሰላምን፣ በጭቅጭቅ የዋለም ተረፈ-ጭቅጭቅን ይዞ መመለሱ አይቀርም፡፡

እናም አንድ ነገር ልብ ማለት ይገባናል (በተለይም አሠሪዎች)፡፡ ሠራተኞች በሥራ ቦታቸው ደስተኛ እንዲሆኑና ውጤታማ አፈፃፀም አስመዝግበው ድርጅታችንን በስኬት ያስጉዙት ዘንድ የሥራ ቦታቸውን ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ ማኅበራዊ ሕይወታቸውን ማየት ያስፈልጋል፡፡ ከሰማይ ወርደው አይደለም ሥራ ቦታ የሚገኙት፡፡ ከምድራዊ ቤታቸው ወጥተው ነው የሚመጡት፡፡ (ያውም መኖሪያ ቤት ካላቸው)፡፡

ባጭሩ አንድ ድርጅት የሠራተኞቹ ሁለንተናዊ ጉዳይ ጉዳዩ ሊሆን ይገባዋል፡፡ የሠራተኞቹን የኑሮ ዋስትና ሳያረጋግጥ የድርጅቱን ቀጣይነትና አትራፊነት ማረጋገጥ አይችልም፡፡ ማኅበራዊ ኑሯቸው የተረበሸ ከሆነ ሥራ ቦታቸውንም ያልተረጋጋ ያደርጉታል፡፡ ደንበኞችን ይረብሻሉ፡፡ ሌት በቤታቸው ጣጣ እንቅልፍ አጥተው ያደሩ ሠራተኞች ቀን በብሩህ አዕምሮ ያገለግላሉ ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው፡፡

አንድ ድርጅት ለሠራተኞቹ ወርሃዊ ደመወዝ ከመስጠት አልፎ ማሰብ አለበት፡፡ ደመወዙ ያኖራቸዋልን? ቤት አላቸው ወይስ ተከራይተው ነው የሚኖሩት? ተከራይተው ከሆነ ከደመወዛቸው ምን ያህሉን ለኪራይ ይከፍላሉ? በዚህ መልኩ እየኖሩ ውጤታማ አገልጋዮች ሊሆኑ ይችላሉ? ይህንን ችግራቸውን ለመቅረፍ የድርጅቱ ሚና ምን መሆን አለበት?..... ወዘተ የሚሉ ጥያቄዎችን መመለስ ያስፈልጋል፡፡ ያለበለዚያ ሠራተኛ ፊቱን ባጠቆረ ቁጥር መቅጣት ብሎም ማባረር፣ ‹‹ስትፈልግ ሥራ ሳትፈልግ ሂድ ሌላ ይመጣል›› ማለት ሁሉ ዘላቂና አስተማማኝ መፍትሔ ሊሆን አይችልም፡፡

‹‹ሠራተኞች ሲኖሩ ብቻ ነው ድርጅቱ የሚኖረው›› የሚለው አባባል በራሱ ትንሽ መስተካል አለበት ባይ ነኝ፡፡ በአንድ ድርጅት ውስጥ ‹‹የሠራተኞች በቁጥር ተሟልተው መገኘት›› ብቻ ሳይሆን ‹‹በትክክለኛ የሥራ መንፈስና በሙያዊ ፍቅር›› መገኘታቸው ነው የድርጅቱን መኖር የሚያረጋግጠው፡፡ ለዚህ ደግሞ ትልቁ የቤት ሥራ ለድርጅቱ የተሰጠ ነው፡፡ በቁጥር የተሟሉ ሠራተኞችን ከመቅጠር ባለፈ በሥራ መንፈስም ማዘጋጀት አለበትና፡፡

‹‹የቤትህን አመል እዛው...›› ከማለት ባሻገር በሠራተኞች ሁለንተናዊ ሕይወት ላይ መሠራት አለበት፡፡ የቤት ችግር ቤት ውስጥ ሊቀር አይችልምና፡፡ ሰውየው በየሄደበት ይከተለዋል፡፡ የአንድ ሰው ጤነኛ አለመሆን ደግሞ የሚረብሸው ራሱን ብቻ አይደለም፡፡ ቤተሰቡን፣ ማኅበረሰቡን አልፎ ተርፎም ሀገርንም ጭምር እንጂ፡፡

የመሪነት ክህሎት ከማጎልበት ይልቅ ሁሌም የበታች እና ‹ተመሪ› ብቻ እንደሆኑ እንዲያስቡ ያደርጓቸዋል፡፡ ይህም በስራ ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተፅዕኖ በማሳደር ድርጅቱን ለውድቀት እና ለኪሳራ ይዳርገዋል፡፡

8. ይቅርታ መጠየቅን አለመልመድ

ሌላው የደካማ መሪዎች መገለጫ ይቅርታ መጠየቅን አለመፈለግ ወይም አለመቻል ነው፡፡ የዚህ አይነት ሰዎች ይቅርታ መጠየቅን ልክ እንደ መሸነፍ ስለሚቆጥሩት በምንም ተዓምር ለየትኛውም ጥፋታቸው ይቅርታን አይጠይቁም፡፡ ይህ ባህርያቸውም ሌሎችን / ሰራተኞቻቸውን/ ከማትጋት ይልቅ ወደ ኩርፊያ እና ግዴለሽነት ይመራቸዋል፡፡

9. ትክክለኛ ያልሆነ ፍረጃ

ስኬታማ ያልሆኑ መሪዎች ሌሎችን ዝቅ አድርጎ በመመልከት ትክክለኛ ያልሆነ ፍረጃ ማድረግ ይወዳሉ፡፡ ምንም እንኳን የሌሎችን አስተያየት እና ምክር ቢፈልጉም የሚያገኙትን አስተያየት ከተናጋሪው የስራ ደረጃም ሆነ ሌላ ተያያዥ ያልሆነ ጉዳይ ጋር በማያያዝ ይፈርጁታል፤

ብዙ ጊዜም የተሰጠውን ሃሳብ ውድቅ ያደርጋሉ፡፡ ይህም ሃሳብ ሰጪውን ሌላ ጊዜ ዝምታን እንዲመርጥ እና ሀሳብ ላለመስጠት እንዲወስን ያደርገዋል፡፡ ይህ ሃሳብን ያለመቀበል ባህርያቸው ለራሳቸውም ሆነ ለሚመሩት ድርጅት ለውጥን ያለመፈለግና ሁል ጊዜም በያዙት መንገድ ብቻ እንዲጓዙ ያደርጋቸዋል፡፡

10. ማመስገንን አለመውደድ

ምስጋናን እንደመሸነፍ የሚቆጥሩት እነዚህ መሪዎች ዓለም የእነርሱ እዳ እንዳለባትና ሰዎችም በጎ ነገር የሚያደርጉላቸው ያንን እዳ ለመክፈል እንደሆነ በማሰብ ከማመስገን ይልቅ “ሥራው በደንብ አልተሰራም፤ በቂ አይደለም” ማለትን ይመርጣሉ፡፡

ይህ ስኬታማ ያልሆኑ መሪዎች ባህርይ እያተጉ ከመምራት አንፃር ከፍተኛ ክፍተት ስለሚኖርባቸው የተከታዮቻቸውን ተነሳሽነት ከማዳከምም በላይ የሞራል ውድቀት በማስከተል በመጨረሻ የድርጅትን ውጤታማነትን ያዳክማል፡፡

References:• GordonTredgold,(Aug10,2016).20HabitsofHighlyUnsuccessfulandIneffectiveLeaders,Retrievedfromhttp://techninja.me• HabitsofUnsuccessfulPeoplevs.SuccessfulPeople,accessedfromhttp://www.skillsyouneed.com• JohnMichaelMorgan(April28,2015).• 10MajorCausesofFailureinLeadership,Retrievedfromhttp://johnmichaelmorgan.com• SydneyFinkelstein,(June2003)• WhySmartExecutivesFail,Penguingroup,USA.

10 ስኬታማ ያልሆኑ... (ከገፅ 26 የቀጠለ)

Page 41: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 37

Life in your 20s is one weird, wild emotional roller coaster. You're finding your first job, getting your first promotion, meeting new friends, and losing old ones. Everything is constantly changing, but don't get stuck feeling like everything is one mistake away from falling apart; the chaos of early adulthood is totally normal.

Instead of being overwhelmed by the changes around you, there are certain tips and tricks that can help you shift your focus and ultimately feel happier. There are so many things that make your 20s an amazing period of time, and it's the good stuff you'll really want to remember. So read on for 25 ideas on how to live a happier, healthier life as the amazing 20-something you are:

Don’t sweats being broke: Almost everyone your age is having a tough time making ends meet.

Have fun for free: Just because you're low on funds doesn't mean you can't enjoy yourself.

Master body language: Learn psychological mind-hacks and read people better.

Make new friends: Meeting new people is hard after college, so give yourself an extra push to be more social.

Build a network: From friends to co-workers, everyone you meet could help you get your next opportunity.

Learn to cook: You'll eat better, feel

accomplished, and save money.

Try new things: You might find a new hobby you never expected to love. Plus, even if you don't love it, you'll at least learn something about yourself.

Do something that scares you: Step out of your comfort zone, whether that means stepping on stage at karaoke night or going out to dinner alone. Always push your personal boundaries.

Learn the difference between true friends and fake friends: Then focus on the people who truly love you, and let the others fall aside.

Accept your mistakes: With so many changes, you're going to make a lot of mistakes. And that's OK.

Step up: Instead of avoiding those mistakes, do your best to learn from them.

Take good care of yourself: Eat healthy, sleep well, and get exercise — it really does make a difference.

Be a little selfish: You deserve to make choices that will help fulfill you.

. . . But not too selfish: Don't knock others down to get to the top, what goes around does come around.

Remember family time: Your elders can offer up some pretty good advice; after all, they lived it first. Plus, if you don't listen now, you might regret it later.

How to Be Happier in Your 20sBy: Hanna Tsegaye

ልዩ ል

Page 42: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ዜና ልማት ባንክ www.dbe.com.et 38

ሴትና ወንድ መሆን ባይቃረን ኖሮአሁን ብንሠራ ባንድ ዓይት ተፈጥሮአስባችሁታል ፆታዊ ኑሯችን…ለምን ይሆን ነበር መፈላለጋችን?…ወንድ ፍጹም የሌለው ባይገኝ ከሴቶችሴት ፍጹም የሌላት ባይገኝ ከወንዶች ስሜት እንደመራን በመትጋት ዘወትር በዚህ ድንቅ መሳሳብ እንፋቀር ነበር?…ምድርንም እንያት…አሁን አለት ብትሆን የተጠፈጠፈችወይም አፈር ብቻ የተፈረፈረችወይም ውኃ ብቻ የተጥለቀለቀችወይም ጫካ ብቻ የተጠቀጠቀችወይም ሜዳ ብቻ የተለጠለጠችወይም ዳገት ብቻ - የተቆለቆለችሙቀት ብቻስ ብትሆን እጅግ ‘ምታቃጥልቀዝቃዛስ ብትሆን በውርጭ የምትቀቅልይማርከን ነበር…. ? ልዩነቷ ደምቆ ውበቷ ተባብሮምድር አንድ ነገር ብቻ ብትሆን ኖሮ?

…አይደንቅም የምድር የፅናቷ ምሥጢር?‹‹እሳት እና ውሃ ነፋስ እና አፈር››ፍጹም ሲለያዩ ግን ፍጹም ተሳስረውአጽንተው ሲያኖሯት እንዲህ አሳምረው……በጥቁር ሰማይ ላይ ጨረቃ ባትደምቅ ከዋከብት ባይኖሩ በብሩህ ሰማይ ላይ ውብ ደመና ባይኖር አዕዋፍ ባይበሩውበትን ፍለጋየእኛ ‹ቀና› ማለት ምን ነበር ምሥጢሩ ?…ማስተዋል ተስኖን ጥላቻ ሸፍኖንማይምነት ደፍኖን ሰው ከመሆን ወጥተን - ደንዝዘን ካልሆነለያይቶ በሚያስውብ - በእርሱ በፈጣሪ ከተከናወነ እንዲህ በልዩነት በዝተን ስንፈጠርመታደል መሆኑ ቢገባን ምን ነበር?…ያገር ጭራም ሆነን - ችግር አሳርሮንበብዙ ግጭት ውስጥ - ፍቅር አስተሳስሮንበነጻነት አምባ - ደምቆ መታየቱ

ልዩነታችን ነው! ምሥጢረ-ጥልቀቱ፡፡…አይታያችሁም…? ‹‹አምላክ በጥበቡ ሊያፋቅረን ሲወድበመለያየት ውስጥ ያዘጋጀው መንገድ››?…..ብዙ ስንለያይ ብዙ ይታየናልብዙ ባየን ቁጥር ያው ብዙ ያምረናልለእኛ ያልተሰጠ - ለሌሎች የናኘውያለ-እነርሱ መኖር ፍጹም ማናገኘውስንት ነገር አለ ?ብዙ ጥበብ አለ!ብዙ ውበት አለ!ብዙ ደስታ አለ! ………..በጥልቅ ላስተዋለ፡፡…ብዙ ስንለያይ በብዙ አናማር’ይልቅ እንዋደድ ከተፈጥሮ እንማርልዩነት ነው ውበት ልዩነት ነው ፍቅር!!! …በምሉዕ ተፈጥሮ - በተጠና መጠንእኛ የሌለንን - በሌሎች ‘ሚሰጠንለያይቶ አፋቃሪ - ፈጣሪ ይመስገን!

Stop comparing your life to other people's Instagram accounts: No one is perfect, no matter how great a filter makes everything look.

Expect change: As hard as it is, your 20 are all about change. Do the best you can to keep your head up and face new challenges head on.

Work hard: Earn respect and set yourself apart by always remembering to do your best. Things won't always work out as you hoped, but if you can say you gave it your best effort, you've accomplished something great.

Talk less, listen more: We all love to share our stories, but the secret to building relationships is letting others speak first. This simple secret will help you connect with the people around you.

Remember not to get too serious: Though you're officially an adult, that doesn't mean you can't have fun or laugh at yourself. Life will feel easier if you learn to take things with a grain of salt.

Pursue what you love: Whether it's your career or your after-work hobby, make sure

there are things in your life that you love. Carving out the time to read, knit, eat cheese — whatever — will make life enjoyable every single day.

Love your body: Learn to look in the mirror and know that you are beautiful. Every so-called imperfection is what makes you unique and interesting, so wear them with confidence!

Travel: Visiting other parts of the world offers you a chance to experience the lives of others and experience situations that teach you new things about yourself. Plus, there are so many beautiful places to see.

Don't pressure yourself to fit an ideal: Everyone is on different tracks through life, and though you may envy the successes of others, learn that it's OK to be different. Your successes cannot be compared to anyone else's.

Appreciate your freedom: Adulthood is full of difficult responsibilities, but a huge upside is the freedom to be yourself and to do what you love. Appreciate how lucky you are to live a life where you can choose your path every day.

ልዩነት=ውበት=ፍቅር(መላኩ አላምረው)

Page 43: ዜና ልማት ባንክ...ዜና ልማት ባንክ 3 On the other hand, high level expertise from Eximbank also introduced and presented about their Knowledge Sharing Program

ግብርናየእርሻ ውጤቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱሰትሪዎችየመፈብረኪያ ኢንዱስትሪዎችየቱር ኢንዱሰትሪዎችየግንባታ ኢንዱስትሪዎችየማዕድን ልማት

ሰፋፊ እርሻዎችየእርሻ ውጤቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱሰትሪዎችየመፈብረኪያ ኢንዱስትሪዎችየማዕድን ልማት ኢንዱስትሪዎች

AgricultureAgro ProcessingManufacturing IndustriesTour IndustriesConstruction IndustriesMining and Quarries

ፕሮጀክት ፋይናንሲንግ | Project Financing

ሊዝ ፋይናንሲንግ | Lease Financing

Commercial AgricultureAgro Processing IndustriesManufacturing IndustriesMining and Extractive Industries